ሰማያዊ ፓርቲ እሁድ ያስመረቀውን ቲያትር በቪሲዲ ለህዝብ ሊያደርስ ነው

 

“ታዋቂ አርቲስቶች አንሳተፍም ማለታቸው አሳዛኝ ነው” ኢ/ር ይልቃል ጌትነት
የመንግስት ሲኒማ ቤቶች ትያትሩን ለማሳየት ፈቃደኛ አልሆኑም
ሰማያዊ ፓርቲ ባለፈው እሁድ ያስመረቀውን “የነፃነት ፈለግ” የተሰኘ ቲያትር በቪሲዲ ለህዝብ ሊያቀርብ እንደሆነ የፓርቲው ሊቀመንበር ኢ/ር ይልቃል ጌትነት ገለፁ፡፡
እሁድ እለት በጣሊያን የባህል ተቋም የተመረቀው ትያትሩ፤ በፕሮፌሽናል ካሜራ መቀረፁንና በቅርቡ ኤዲቲንጉ አልቆ በቪሲዲ ለህዝብ እንደሚደርስ የጠቆሙት ኢ/ር ይልቃል፤ ትያትሩን በመንግስት ሲኒማ ቤት ለማሳየት ሲኒማ ቤቶች ፈቃደኛ ባለመሆናቸው በቪሲዲ ለማውጣት ተገደናል ብለዋል፡፡ 
የ70 ደቂቃ ርዝመት ያለው ትያትሩ በአገሪቱ ወቅታዊ የፖለቲካና ማህበራዊ ችግሮች ላይ የሚያተኩር መሆኑንና የፓርቲው አባል በሆነው ወጣት ዳዊት ፀጋዬ እንደተፃፈ የተናገሩት ኢ/ር ይልቃል፤ ታዋቂ አርቲስቶች በትያትሩ ላይ ለመሳተፍ ለሶስት ወራት ሲለማመዱ መቆየታቸውን ጠቁመው፤ በኋላ ግን መንግስትን በመፍራት ጥለው እንደወጡና በዚህም እርሳቸውና ሌሎች የፓርቲው አባላት እንዳዘኑ ገልፀዋል፡፡ “ታዋቂ አርቲስቶች ሙያቸውን በመጠቀምና ለእውነት በመቆም ህዝቡን ማገልገል አለባቸው” ያሉት ኢ/ር ይልቃል፤ ታዋቂ የትያትር አዘጋጅና አስተማሪ የሆነው ግለሰብ “ሀላፊነት አልወስድም” ብሎ ዝግጅቱን አቋርጦ ከአገር መውጣቱንም ገልፀዋል። “አዘጋጁ ሀላፊነት አልወስድም” ያለው በተለይ ግንቦት ላይ ሰላማዊ ሰልፍ በማድረጋችንና ጉዳዩ መነጋገሪያ በመሆኑ ነው” ብለዋል፡፡ 
“ተዋንያኑም አዘጋጁን አምነን ነው ስራውን የጀመርነው፤ እርሱ ሀላፊነቱን ካልወሰደ እኛም አንፈልግም” በማለት ከሶስት ወር በኋላ ጥለው መበተናቸውንና እንደ አዲስ ሌሎች ወጣት ተዋንያንና አዘጋጅ ተፈልገው ልምምዱ መጀመሩን የገለፁት የፓርቲው ሊቀመንበር፤ በዚህ ምክንያት ቴያትሩን ለእይታ ለማብቃት ከስድስት ወር በላይ መፍጀቱን ገልፀዋል። ትያትሩ ትርፍን ማዕከል ባላደረገ መልኩ የተዋንያን እና የደራሲውን ወጪ ለመሸፈን በመጠነኛ ዋጋ ለህዝብ ይደርሳል ያሉት ሊቀመንበሩ፤ ፓርቲዎች ለአጭር ጊዜ ገቢ ማስገኛ ስራዎችን የመስራትና ለገበያ የማቅረብ መብት እንዳላቸው አዋጁ እንደሚደነግግ ገልፀው፤ ቪሲዲውን በቅርቡ ለማከፋፈል ዝግጅት እየተጠናቀቀ እንደሆነ አብራርተዋል፡፡ ትያትሩ በተመረቀ እለት ፕሮፌሰር መስፍን ወ/ማርያምን ጨምሮ በርካታ ሰዎች ተገኝተው አድናቆታቸውን መግለፃቸውን የተናገሩት ኢ/ር ይልቃል፤ ሥራው በተቃዋሚ ፓርቲ ደረጃ የመጀመሪያና አስተማሪ መሆኑን ፕሮፌሰሩ መናገራቸውን አውስተዋል፡፡ 
ፓርቲው ትያትሩን በመንግስት ሲኒማ ቤት ለማሳየት ፈልጎ ይሁንታ በማጣቱ በጣሊያን የባህል ተቋም ካስመረቀ በኋላ ተቋሙ ለትያትሩ ደራሲ “አገባባችሁ ትክክል አይደለም፣አታላችሁናል፣ አዳራሹም ለፖለቲካ ስራ ውሏል” የሚል ይዘት ያለው ደብዳቤ መፃፉን የተናገሩት ኢ/ር ይልቃል፤ በዚህም ማዘናቸውን ገልፀዋል፡፡

addis admas

posted by Aseged Tamene

ኃይሌ ገብረ ሥላሴ ፊቱን ወደ ወርቅ ማዕድን አዞረ

ኃይሌ ገብረ ሥላሴ ፊቱን ወደ ወርቅ ማዕድን አዞረ

-በ29 ሺሕ ካሬ ሜትር ውስጥ ወርቅ ለማምረት ማስጠናት ጀምሯል

ታዋቂው አትሌት ኃይሌ ገብረ ሥላሴ ከፍተኛ ኢንቨስትመንት በሚጠይቀው የማዕድን ዘርፍ ውስጥ በመግባት፣ በደቡብ ክልል ለወርቅ ማምረቻ በተረከበው ቦታ ላይ የመጀመሪያ ደረጃ ጥናት ማጠናቀቁ ታወቀ፡፡

ከሌሎች ኢትዮጵያውያን ጋር በመሆን በሽርክና ወርቅ ለማምረት የተቋቋመው አዲሱ ኩባንያ ላጋሉላ የሚል ስያሜ አለው፡፡ የኩባንያው ስያሜ የተወሰደው ለወርቅ ማምረቻ ከተመረጠው አካባቢ መጠሪያ ነው፡፡ አዲሱ ኩባንያ ለመጀመሪያ ደረጃ ጥናቱ የተረከበው መሬት 29 ሺሕ ካሬ ሜትር መሆኑን፣ በቅርቡም ተጨማሪ ቦታ ለመጨመር ዕቅድ እንዳለው ኃይሌ ለሪፖርተር ገልጿል፡፡ ወርቅ በማምረት ታዋቂ ከሆነ አንድ የደቡብ አፍሪካ ኩባንያ ጋር ድርድር እያደረገ መሆኑንም ለማወቅ ተችሏል፡፡

በአሁኑ ጊዜ የመጀመሪያ ደረጃ ጥናቱ የተጠናቀቀ በመሆኑ፣ ቀሪ ሁለት ጥናቶች ከተካሄዱ በኋላ ወደ ምርት ይገባል፡፡ ወርቅ ማምረት ከፍተኛ ኢንቨስትመንት የሚጠይቅ መሆኑን የገለጸው ኃይሌ፣ የፈለገውን ያህል ወጪ ቢጠይቅ በዚህ ዘርፍ በመሰማራት የአገሪቱን የወጪ ንግድ ለማሳደግ የበኩሉን አስተዋጽኦ ለማበርከት መቁረጡን አስረድቷል፡፡

የአገሪቱ የወደፊት አቅጣጫ በወጪ ንግድ ላይ የተመሠረተ መሆን አለበት የሚል እምነት እንዳለው የሚገልጸው ኃይሌ፣ ወደ ወርቅ ምርት ኢንቨስትመንት ለመግባት ባደረገው ጥናት አገሪቱ ከፍተኛ የሆነ የወርቅ ሀብት እንዳላትና አዋጭ የሆነ የኢንቨስትመንት ዘርፍ እንደሆነ መመልከቱን አስታውቋል፡፡

አትሌቱ በዘርፉ በማድረግ ያለውን እንቅስቃሴ የጀመረው ላጋሉላ የወርቅ ማምረቻ ኩባንያ ከመቋቋሙ ቀደም ብሎ የቡናና የቅመማ ቅመም እርሻ ሲጀምር መሆኑን ገልጿል፡፡ ለዚሁ የእርሻ ኢንቨስትመንቱም በደቡብ ክልል ማሻ ወረዳ ከ1,500 ሔክታር መሬት በላይ መረከቡ ይታወሳል፡፡ እስካሁንም ለእርሻ ሥራው ከ70 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ ማድረጉንና ከ400 በላይ የሚሆኑ ሠራተኞችን መቅጠሩን ይናገራል፡፡

በአሁኑ ወቅትም በ200 ሔክታር መሬት ላይ የቡና ተከላ መጀመሩ ተገልጿል፡፡ አትሌት ኃይሌ አዲሱን ኩባንያ ሳይጨምር አሁን በተሰማራባቸው የሆቴል፣ የሪል ስቴትና ሌሎች የተለያዩ መስኮች ከአንድ ቢሊዮን ብር በላይ ኢንቨስትመንት እንደሚያንቀሳቅስ ይነገራል፡፡

posted by Aseged Tamene

“አዜብን ማሰር፣ መለስን ከሞት ቀስቅሶ ለፍርድ ማቆም ነው”

መለስ ዜናዊ ሆን ብለው ለፖለቲካ ሚዛን መጠበቂያ ሲገለገሉበት በነበረው “የሙስና ባህር” ያልተነከረበት የለም። ባህሩ ውስጥ ያልዋኘ የለም። ከባህሩ ራሳቸውን ያገለሉ ጥቂቶች ቢኖሩም ወ/ሮ አዜብ መስፍን ግን የባህሩ ዋናው አጥማቂና የውሃው ባለቤት እንደሆኑ በርካታ ምስክሮች አሉ።

አቶ መለስ “ውርሳቸውን/ሌጋሲያቸውን” ትተው ካለፉ በኋላ አገሩን አከርፍቶት የነበረው የሙስና ባህር በስንጥር መነካካት ተጀመረና አሁን ቁንጮዎቹ ግድም ደርሶ እያሸበረ ነው። ይህንኑ የሙስና ማዕበል ተከትሎ የባለቤታቸውን ውርስ ታኮ ያደረጉት ወ/ሮ አዜብና በተሸናፊው የፖለቲካ መስመር ያሉ ሁሉ ተሸብረዋል። አንዳንድ ጥቆማዎችና የህዝብ አስተያየቶች እንደሚያመለክቱት ወ/ሮ አዜብ ታውከዋል።

ከገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን ሃላፊዎችና ከነሱ ጋር በተያያዘ በቁጥጥር ስር ከዋሉት “ባለሃብቶች” መካከል ከወ/ሮ አዜብ መስፍን ጋር እንደሚነግዱ የሚታወቁ በቁጥጥር ስር መዋላቸው የስጋታቸው መነሻና እምብርት ስለመሆኑ አብዛኞች ይስማማሉ። ከዚህም በተጨማሪ ያለታክስ በሚገቡ ምርቶች፣ ተሽከርካሪዎች፣ በቴሌ የህገወጥ ማስደወል ወንጀል፣ በጫት ኤክስፖርትና በኮንስትራክሽን ዘርፍ በስፋት ቢዝነስ እንደሚያጫውቱ የሚታወቁት ወ/ሮ አዜብ በገንዘብ የከበሩትን ያህል በርካታ ጠላት እንዳፈሩም የሚቀርቧቸው ይናገራሉ።

azeb 2ኤፈርትን ለወ/ሮ አዜብ ያስረከቡት አቶ ስብሃት ነጋ በተደጋጋሚ ስለሙስና መናገር የጀመሩት አቶ መለስ አፈር ሳይቀምሱ ነበር። ወ/ሮ አዜብ የባለቤታቸውን ጡንቻና በዘመቻ በጀት ተመድቦለት “ባለራዕይ፣ ታላቁ መሪ” በሚል የተሰጣቸውን የሸቀጥ ስም ተገን አድርገው ሙስና ውስጥ መነከራቸውን የሚያውቁት አቶ ስብሃት ስም አይጥቀሱ እንጂ ነገራቸው ሁሉ ከወ/ሮ አዜብ ደጅ እንደነበር ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው የሚናገሩት የአደባባይ ምስጢር ነው።

አቶ ስብሃት ነጋ ከመለስ ሞት በኋላ ይህንኑ አቋማቸውን አጠንክረው የገፉበት ቢሆንም በፖለቲካ አሰላለፋቸው ተሸናፊ በመሆናቸው ለማፈግፈግ ተገደው እንደነበር የሚናገሩ አሉ። ከውስጥ አዋቂዎች እንደሚሰማውና በተባራሪ እንደሚነገረው አቶ ስብሃት ዳግም አሸናፊውን ቡድን ተመልሰው ተቀላቅለዋል። ለዚህም ይመስላል እሳቸው ምን ያህል የጸዱ ስለመሆናቸው መረጃ ባይኖርም አሁን ከተጀመረው የሙስና ዘመቻ ጀርባ እንዳሉበት የሚጠቆመው። አንዳንዶች እንደሚሉት ህወሃት በትከፋፈለ ጊዜ (ዘመነ ህንፍሽፍሽ) አቶ አባይ ጸሐዬ ውህዳኑን ተቀላቅለው መረጃ ከሰበሰቡ በኋላ አቶ መለስን በመቀላቀል የተጫወቱትን የ”መንታ”/ደብል/ ስልት፣ የመለስ ሞትን ተከትሎ ለተነሳው የሃይል ሰልፍ ትንቅንቅ አቶ ስብሃት ነጋም ተጠቅመውበታል። በዚሁ ስልታዊ አካሄድም የእነ ዶ/ር ደብረጽዮን ክንፍ አሸናፊ ሆኖ እንዲወጣ አስችለዋል።

አዜብ መስፍን ለምን አይታሰሩም?

ከሙስና ጋር ስማቸው በስፋት የሚነሳው ወ/ሮ አዜብ፤ በባለቤታቸው እንደ ቪኖ ቡሽ ድንገት ሲፈተለኩ በሃዘን ድባብ ውስጥ ሆነው የጀመሩት ዘመቻ የቀልድ መሃላ ይዘት ያለው ነው። በ”ፖለቲካ ቁጭ በሉ” እንዲመለኩ የተደረጉትን አቶ መለስን ደጋግሞ በመጥራት አዜብ መስፍን “የመለስ ራዕይ ካልተቀየረና ሌጋሲው እስካልተበረዘ ድረስ …” እያሉ ካድሬውንና ቀሪውን የህወሃት ሰዎች መማጸን ላይ አተኩረው ነበር። በሄዱበትና ባገደሙበት የባለቤታቸው ስምና ዝና ላፍታም ካንደበታቸው የማይለያቸው ወ/ሮ አዜብ ጀርባቸውን ስለሚያውቁት የመለስን ስም የሚያንጠለጥሉት ራሳቸውን ለመከላከል እንደሆነም ከታች እስከ ላይ ስምምነት አለ።

ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ ከደረሱት አስተያየቶች መካከል “ካድሬው ባብዛኛው፣ የበላይ አመራሩ በከፊል አዜብስ?” በማለት ለምን በቁጥጥር ስር እንደማይውሉ የሚጠይቁትና የሚነጋገሩት በገሃድ ነው። ይሁን እንጂ አዜብ ለምን እንዲታሰሩ የፍርድቤት ትዕዛዝ (ዋራንት) አይቆረጥባቸውም? ለሚለው የሚሰጠው መልስ “የመለስ ሌጋሲ እንዳይወድም፣ እንዳይቆሽሽ፣ የተሰራው የረከሰና የሸቀጥ ያህል በፖለቲካ ውዳሴ የተገነባው ከንቱ ዝና እንዳይቆሽሽ፣ ብሎም ሌላ ጥያቄ እንዳያስነሳ ነው” የሚል ነው።azeb 1

አቶ ስብሃት ሲመሩት የነበረው ኤፈርትን በሳቸው አዲስ አመራርና በመለስ ልዩ አመራር ሰጪነት በሺህ ለሚቆጠሩ የትግራይ ልጆች የስራ እድል ማዘጋጀቱን፣ ትግራይ ውስጥ በርካታ ፋብሪካዎች እንደሚከፈቱና ሲደበቅ የነበረው በጀት በዶላር ተሰልቶ ለህዝብ ይፋ እንዲሆን በማድረግ ስብሃት ነጋን የማሳጣት እጅ አዙር ዘመቻቸውን አጣድፈው የጀመሩት ወ/ሮ አዜብ የትግራይን ህዝብ ልብ ለማግኘትና አቶ ስብሃት የሚከፍቱባቸውን ዘመቻ አስቀድሞ ለመቋቋም በማሰብ ነበር።

ህወሃት የክልሎችን በጀት እልብ አድርጎ የሚጠባበት የብር ማሽኑ የሆነውን ሜጋ ኢንትርፕራይዝን ይመሩ የነበሩት ወ/ሮ አዜብ መስፍን ከምርጫ1997 በኋላ በድርጅት አቋም፣ በአቶ መለስ ፊርማና ውሳኔ እንዲነሱ መደረጉን፤ ከሃላፊነት የተነሱበት ደብዳቤ እንደደረሳቸው አኩርፈው ወደ ሳዑዲ አረቢያ ሄደው “በሽማግሌ” ከባለቤታቸው ጋር እንደታረቁ፣ ሽምግልናውን ባከናወኑት ሰው አማካይነት ወ/ሮ አዜብ የተነጠቁት ሹመት እንዲመለስላቸው መደረጉን እንደሚያውቁ የሚናገሩ ክፍሎች “ኢትዮጵያ ውስጥ ህግና ፍትህ ለሰከንድ ቢተገበር ህገወጥ ስልክ በማስደወል የሜጋን ቢሮ ለዋና ማቀናበሪያና የተጠቀሙበት ወ/ሮ አዜብ የመጀመሪያዋ ተጠያቂ ሊሆኑ በተገባ ነበር። የመለስ ሌጋሲ እንግዲህ ይህን ነው” በማለት ይጠይቃሉ።

እነዚህ ክፍሎችም ሆኑ ሌሎች ወገኖች አዜብ መስፍን የፖለቲካ ሃይላቸው የተቦረቦረ፣ ከበዋቸው የነበሩት ሃይሎች የተመናመኑ፣ እንደ ተርብ የሚናደፈው አንደበታቸውና ባህሪያቸው እንደበረዶ የቀዘቀዘበት ወቅት ላይ እንደሚገኙ እየተገለጸ ነው። በጸለመ ልብስ የሚታዩትና የሃዘን ጥቁር ልብሳቸውን ለመቀየር ፈቃደኛ ያልሆኑት ወ/ሮ አዜብ ተቅለስላሽ ሰው ሆነው መታየታቸው ስጋታቸው ማየሉን የሚያሳይ እንደሆነ የሚመሰክሩት ክፍሎች “አዜብ መስፍን ወዳጅ እንደሌላቸውና በተለይም በህወሃት ሰዎችና ካድሬዎች ዘንድazeb-mesfinስለማይወደዱ ዙሪያቸውን ከሚዞራቸው የሙስና ደወል ማምለጥ ስለሚችሉበት ሁኔታ ሊያስቡ እንደሚችሉ እንገምታለን” ይላሉ። ለአብነትም ሲያኮርፉ ወደ ሳዑዲ እንደሚሄዱና በዱባይ ሪል ስቴት እንዳላቸው ስለሚታሙ ጓዛቸውን ጠቅልለው ወደዚያው ሊያመሩ እንደሚችሉ ምልክት እንዳለ ይጠቁማሉ። በዱባይ አላቸው ስለሚባለውና በሌሎች ተቋራጭ ድርጅቶች ስም ስለተገነቡት ቤቶችና ንብረቶቻቸው እነዚህ ክፍሎች ለጊዜው ዝርዝር አስተያየት ከመስጠት ተቆጥበዋል።

በሌላ ወገን ግን አሁን የባለቤታቸውን የፋውንዴሽን ስራ እንዲሰሩ የተመደቡት ወ/ሮ አዜብ የእነ በረከት ስምዖን ቡድን በመሆናቸው፣ ለዚሁ ቡድን ቀኝ እጅ የሆኑት የደህንነቱ አውራ አቶ አሰፋና ሸራተን ያሉት ባለሃብት እጅግ ወዳጃቸው በመሆናቸው ቀስ በቀስ እንዲከስሙ ይደረጋል እንጂ አይታሰሩም ሲሉ በድፍረት ይናገራሉ። ወ/ሮ አዜብን ማሰር ማለት አቶ መለስን ከመቃብር አውጥቶ እንደገና ፍርድ አደባባይ የማቅረብ ያህል እንደሆነ የሚናገሩት እነዚህ ክፍሎች “ታላቁ፣ ባለራዕዩ፣ አስተዋዩ፣ አርቆ አሳቢው፣ የደሆች አባት፣ ራሱን ‘ለኢትዮጵያ’ አንድዶ የሞተ፣ አንዲት ሃሳብ ይዞ ወደ (ኢትዮጵያ) ምድር የመጣው አዳኝ፣ እረፍት የማያውቀው፣ ዜጎቹን በቀን ሶስቴ እንዲበሉ ያስደረገው፣ የአፍሪካ አንደበት፣ የዓለም ቅርስ፣ የወደፊቱ ኢትዮጵያ ተምሳሌት፣ የታሪክ አውራ፣ እርምና ወንጀል የሌለበት … በማለት ህወሃት ሆን ብሎ የገነባውን ስም አዜብን በማሰር አፈር አይከተውም” በማለት አዜብ ሊታሰሩ የማይችሉበትን ምክንያት ያመላክታሉ።

የመጨረሻው መጀመሪያ

birhane

ብርሃነ ኪዳነማርያም

ወ/ሮ አዜብ የመጨረሻው መጀመሪያ ላይ ስለመሆናቸው ምልክቶች እንዳሉ የሚጠቅሱ አሉ። ያለ ከልካይ ሲመሩትና ሲነዱት ከነበረው ግዙፉ የህወሃት የገንዘብ ቋት ኤፈርት ተሰናብተዋል። ወንበራቸውን እንዲቀሟቸው የተደረጉት የዋልታ ኢንፎርሜሽን ዋና ስራ አስኪያጅና የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ፕሬዚዳንት የሆኑት ብርሃነ ኪዳነማርያም (ብርሃነ-ማረት) የቀድሞው የፍቅር ወዳጃቸው ናቸው። በደህንነት ውስጥ አድራጊና ፈጣሪ የነበሩት የቅርብ የንግድ ሸሪካቸው አቶ ወልደስላሴ ወልደሚካኤል በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው የሚጠየፉትን ወህኒ ገብተውበታል። በከፍተኛ የንግድ ቅርርብና ሽርክና የሚወዳጇቸው አቶ ነጋ ገብረ እግዚአብሔር ከታሰሩ ወራት ተቆጥሯል። የገቢዎችና ጉምሩክ ምክትል ዳይሬክተር የነበሩት አቶ ገብረዋህድ ከቀረጥ ነጻ በመፍቀድ አብረዋቸው በኤፈርት ታርጋ ገንዘብ ሲያልቡ ኖረው አሁን ወደ እስር ቤት ተወርውረዋል። የቴሌ የሙስና ቅሌትና በኦሮሚያ የመሬት ንግድ አብረዋቸው ሲሳተፉ የነበሩ ሁሉ ዋራንቲ ተቆርጦባቸው እስር ቤት ገብተዋል። እንግዲህ በዚህ ሁሉ መዓት ውስጥ ያልተነኩት ወ/ሮ አዜብ ብቻ ናቸው።

ለፌደራል የጸረ ሙስና ኮሚሽን ቅርብ የሆኑ ምንጮች እንደሚሉት ተጠርጣሪዎቹ በምርመራ ወቅት ወ/ሮ አዜብን በትዕዛዝ ሰጪነትና በንግድ አጋርነት ዋና ተባባሪ መሆናቸውን በማመልከት መስክረዋል። ከዚህም በላይ በርካታ ጥቆማ አለ። በነዚህና በበርካታ ምክንያቶች ጣት የተቀሰረባቸው ወ/ሮ አዜብ አሁን የቀብርና የተስካር፣ ሙት ዓመት ዘካሪና የማስታወሻ ግንባታ ኮሚቴ ሃላፊ ሆነው ተቀምጠዋል። የመጀመሪያው መጨረሻ “መገለል” እንደሆነ፣ ከዚያም እውነተኛው መጨረሻ ሊገጥማቸው እንደሚችል ግምታቸውን የሚሰጡ ተበራክተዋል። “ከቶውንም አይታሰሩም። ለመለስ ሲባል “የሚሉት ደግሞ መጨረሻቸው ከኢህአዴግና አሁን ካለው የቡድን ፍትጊያ ጋር እንደሚሆን ይናገራሉ።


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (http://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

posted by Aseged Tamene

ጓደኛውን በገጀራ ቆራርጦ የጣለው ጉዳዩ በፍርድ ቤት እየታየ ነው

በተስፋሁን ብርሃኑ
ፖሊስና ርምጃው

‹‹እኔ ስራ አስገብቼው ሳለ ለአለቃዬ ዘወትር ስለ እኔ መጥፎ ነገር ይናገራል ያለውን ጓደኛውን ሶስት ቦታ ቆራርጦ የጣለው በፍርድ ቤት ጉዳዩ እየታየ ነው፡፡

ተጠርጣሪ ሀጎስ ገብሩና ሟች አምሳሉ ምትኩ በአራዳ ክፍለ ከተማ ቀበሌ 11/12 ልዩ ቦታው አራት ኪሎ ዩንቨርሳል ቴክኖሎጂ ኮሌጅ ውስጥ በጥበቃ ስራ ላይ ተሰማርተው ይገኙ ነበር፡፡ ተጠርጣሪው ‹‹ዋና ፀባችን ነው ያለው እኔ ስራ አስገብቼው ልወደድ በማለት ዘወትር ስለ እኔ መጥፎ ነገር መናገርና እያመሸ እየመጣ ስራ ተበድሏል በማለት ያጣላኝ ነበር›› ብሏል፡፡ በምርመራ ወቅት፡፡ ይሄኔ ቂም የያዘው ተጠርጣሪ ሀጎስ ገብሩ ከሁለት ወር በፊት ለግድያ መዘጋጀት ይጀምራል፡፡

ለግድያ የሚያስፈልገውንም ከብረት የተሰራ ገጀራ ከመርካቶ እንደገዛ ተናግሯል፡፡ ሟች አምሳሉ ሲመጣ ‹‹እባክህ ራት በልቼ ልምጣ ስለው ባትበላ ምን አገባኝ አፈር ብላ ብሎኝ ወጣ›› ይላል ተጠርጣሪው በምርመራ ወቅት፡፡ ሟች በዚሁ ቀን አምሽቶ ሲመጣ በደሉ በዛብኝ ያለው ተጠርጣሪ በሩን ከከፈተለት በኋላ ሟችን በሩን እንዲዘጋው ከነገረው በኋላ ፊቱን ወደ በሩ ሲያዞር በያዘው ገጀራ ፊቱን ይመታዋል፡፡ ከዚያም ከመሬት ከወደቀ በኋላ አንገቱ አካባቢ ሲመታው ህይወቱ ሊያልፍ መቻሉ ተገልጿል፡፡

ተጠርጣሪው የሟችን አስክሬን ውሃ ወዳለበት ቦታ በመውሰድ በገጀራው ወገቡንና ሁለት እግሮቹን ቆራርጧል፡፡ ከወገብ በላይ አራት ኪሎ አካባቢ በሚገኝ ድልድይ መሻገሪያ ውስጥ የጣለው ሲሆን ግራና የቀኝ እግሩን ደግሞ በቢጫ ኩርቱ ፌስታል ጠቅልሎ የሚሰሩበት አካባቢና ብርሐንና ሰላም ማተሚያ ቤት ከፍ ብሎ በሚገኘው ሳጠራ ጠጅ ቤት አካባቢ ሊጥለው ችሏል፡፡ የአዲስ አበባ ፖሊስ የሰው መግደል ወንጀል መርማሪ ቡድን ወንጀሉ በተፈፀመ ሰሞን ከህብረተሰቡ ጋር በተደረገ ቅንጅት ተጠርጣሪውን በቁጥጥር ስር ሊያውሉት ችለዋል፡፡ መርማሪ ግሩም ታረቀኝ የአዲስ አበባ ፖሊስ የግድያ ወንጀል መርማሪ አስፈላጊውን የሰውና የሰነድ ማሰረጃ አሰባሰበው ካጠናቀቁ በኋላ ለከፍተኛው ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ችሎት መዝገቡን ልከው ውሳኔ በመጠባበቅ ላይ ይገኛሉ፡፡

freedom4ethiopian

posted by Aseged Tamene

በሹመኛ የመጅሊስ አባላትና በመንግስት መካከል አለመግባባት መንገሱ ተሰማ!! (ድምፃችን ይሰማ)

ረቡእ ነሐሴ 22/2005
‹‹የሕግ ጉዳይን ለሕግ ትተን አክራሪዎችንና ጽንፈኞችን በሰላማዊ ሠልፍ እናወግዛለን››  የሃይማኖት ተቋማት ጉባዔ ተወካዮች

አንዳንድ የወረዳ መጅሊስ ሹመኞች ‹‹መንግስት በሚያዘጋጀው ሰልፍና ስብሰባ ዲናችንን አናሰድብም›› የሚል አቋም ይዘዋል!
 
በመጪው እሁድ ነሀሴ 26 መንግስት በግዳጅ ሊያካሄደው ካሰበው ሰልፍ ጋር በተገናኘ በሹመኛ የመጅሊስ አባላትና በመንግስት መካከል አለመግባባት መፈጠሩ ተሰማ፡፡ አለመግባባቱ የተፈጠረው በመንግስት የቅስቀሳ ስብሰባዎች ላይ በእስልምና ሃይማኖት ላይ ተደጋጋሚ ዘለፋ እና የማንቋሸሽ ተግባራት በመበራከቱና መንግስትም ሁኔታውን ለመግታት ፈቃደኛ ባለመሆኑ እንደሆነ ተነግሯል፡፡ ባለፈው እሁድ የመንግስት ሀላፊዎች ከመጅሊስ የወረዳ ሹመኞች ጋር ባደረጉት ስብሰባ እና ግምገማ የመጅሊሱ ሹመኞች ለመጪው እሁድ የመንግስት ሰልፍ በቂ ቅስቀሳ እያደረጉ እንዳልሆነና ይህ መስተካከል እንዳለበት ያሳሰቡ የመንግስት ሀላፊዎች የሰጡትን ገለጻ ተከትሎ ሹመኞቹ ባደረጉት ንግግር ‹‹በየስብሰባው የሚገኙ የመንግስት ሰዎች ዲናችንን እየተሳደቡብን ሞራላችን እየተነካ ነው›› ያሉ ሲሆን ‹‹በዚህ አቅጣጫ ህብረተሰቡ አግልሎን በዚህ በኩል ደግሞ መንግስት ዲናችንን እያሰደበብን ከመሀል ሆነን እየተጎዳን በመሆኑ መንግስት ዘለፋውን ያስቁምልን›› ሲሉ ጠይቀዋል፡፡
 
በስብሰባው የተገኙ የመንግስት ሀላፊዎች በበኩላቸው የመጅሊሱን ሹመኞች በሰጡት አስተያየት ምክንያት የገሰጿቸው ሲሆን ተሳታፊዎች የፈለጉትን አስተያየት የመሰንዘር መብት አላቸውም ብለዋል፡፡ የመጅሊስ ሹመኞቹ ‹‹ካድሬዎቹ እየሰጡ ያሉት ስሜታዊ አስተያየት ሙስሊሙን እየጎዳ ስለሆነ ሊቆም ይገባል›› በሚል መረር ያለ ወቀሳ ቢያቀርቡም የመንግስት ሀላፊዎች ‹‹የሀገር ጉዳይ ስለሆነ ማንም በስሜት ቢናገር አይፈረድበትም›› በሚል ምላሽ ሰንዝረዋል፡፡ ሀላፊዎቹ አክለውም ሰልፉ ወሳኝ ምእራፍ የሚከፈትበት በመሆኑ ሁሉም የመጅሊስ አባል ከነቤተሰቡ መሳተፍ እንዳለበት አስጠንቅቀው ሰልፉ መንግስት ጠላቶቹን የሚለይት በመሆኑ በሰልፉ አለመሳተፍ የሚያስከፍለው ዋጋ ከፍተኛ እንደሆነ በዛቻ መልክ አስረድተዋል፡፡ ባለፈው ሳምንት በስድስት ኪሎ ስብሰባ ማእከል የአዲስ አበባ ፍትህና ጸጥታ ቢሮ ባዘጋጀው ስብሰባ ተሳታፊ የመንግስት ካድሬዎች የእስልምናን ክብር የሚያራክሱ ዘለፋዎችና የእምነቱን ተከታዮች ክብር የሚያናንቁ ውንጀላዎች መሰንዘራቸውን መዘገባችን የሚታወስ ሲሆን በርካታ የመጅሊስ ሹመኞችም አንገታቸውን ደፍተው ከስብሰባው ለመውጣት ተገደዋል፡፡
 
ይህ በእንዲህ እንዳለ ሰኞ እለት ከቀኑ አስር ሰአት ላይ የክፍለ ከተማ ሃላፊዎች በዚሁ ሰልፍ ጉዳይ ላይ ከየወረዳው መጅሊስ ሹመኛ አባላት ጋር ተመሳሳይ ይዘት ያለው ስብሰባ ያደረጉ ሲሆን በዚህም ስብሰባ መንግስት አስደንጋጭ ሪፖርት ቀርቦለታል፡፡ በተለይም በየካ፣ በአራዳ፣ አዲስ ከተማና ቦሌ ክፍለ ከተሞች ያሉ አንዳንድ የመጅሊስ አባላት ባቀረቡት ሪፖርት አባላቱ እንኳን ታች ወርደው ህብረተሰቡን ለመቀስቀስ ቀርቶ የራሳቸው የመጅሊስ አባላቶች እንኳ ለመሳተፍ ፈቃደኞች እንዳልሆኑና ‹‹መንግስት በሚያዘጋጀው ሰልፍና ስብሰባ ዲናችንን አናሰድብም›› የሚል ምላሽ እንዳቀረቡ ታውቋል፡፡ የመጅሊስ ሹመኞቹ የሰልፍ ተሳታፊዎችን ቃል እንዲያስገቡበት በመንግስት በተሰጣቸው ፎርም ምን ያህል ሰው እንዳሰፈሩ የመረመሩት የመንግስት ሀላፊዎች አንዳንዱ እራሱንና ቤተሰቦቹን ብቻ ያስመዘገበ መሆኑና ሌሎቹ ደግሞ ባዶ ወረቀት ማስረከባቸው ሀላፊዎቹን በብስጭት እንዲወራጩ አድርጓቸዋል፡፡
 

ይህ ሁኔታ ያስደነገጣቸው የመንግስት የክፍለ ከተማ አመራሮች ከዚህ በኋላ የየወረዳ ካቢኔ አባላት ከመጅሊስ ሹመኞች ጋር አብረው እየዞሩ ጥሪ እንዲያቀርቡና ጉዳዩም የሞት ሽረት መሆኑን አስረድተዋል፡፡ ‹‹ይህ ሰልፍ እንዲሳካ እባካችሁ የምትችሉትን ሁሉ አድርጉ›› በሚል በተማጽኖ ጭምር ትእዛዝ ሲሰጡ የነበሩት የመንግስት ሀላፊዎች የመጅሊስ ሹመኞች ጥሪውን ሲያካሄዱ ሃይማኖታዊ አለባበስን ተግባራዊ እንዲደርጉ አዘዋል፡፡ ‹‹ይህ ሰልፍ ከተሳካ ቀጣዩ ስራችን መስጂዶችን ከሙስሊሙ እየነጠቅን ለናንተ ማስረከብ ነው የሚሆነው›› ብለውም ንግግራቸውን አሳርገዋል፡፡ በአዲስ አበባ ደረጃ ቀጣይ ሪፖርት ለመስማት እና ለመገምገም ነገ ሐሙስ ስብሰባ ይኖራል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ እሁድ የሚካሄደውን የግዳጅ ሰልፍ የሃይማኖቶች ጉባኤ ነው ያዘጋጀው በሚል መንግስት ቢገልጽም ሰልፉን ሙሉ በሙሉ መዋቅሩን በመጠቀምና ከፍተኛ ፋይናንስ በማፍሰስ እያስተባበረ ያለው መንግስት መሆኑ ይታወቃል፡፡
posted by Aseged Tamene