የኢትዮጵያ ብ/ቡድን አሰልጣኝ ዮሀንስ ሰሀሌ አሰልጣኝ ሆነው እንዲቀጠሩ ቀጭን ትእዛዝ የሰጡት ጄ/ል ሳሞራ የኑስ ናቸው።

የኢትዮጵያ ብ/ቡድን አሰልጣኝ ዮሀንስ ሰሀሌ ቡድኑን ከመረከባቸው በፊት በደደቢት አሰልጣኝ ሆነው እንዲቀጠሩ ቀጭን ትእዛዝ የሰጡት ጄ/ል ሳሞራ የኑስ ናቸው። የብ/ቡድኑ ስፖንሰር ዋልያ ቢራ ነው። በካምፓኒው ማርኬቲንግ ክፍል የምትሰራ ሴት የዮሀንስ የፍቅር ጓደኛ ናት። በዝች ሴት በኩል ሁሴን አብዱልቀኒና ዳዊት የተባሉ የስፖርት ጋዜጠኞች ገንዘብ እየተዛቀ ይሰጣቸዋል። በራዲዮ “ሽንፈቱ ምንም ማለት አይደለም።ዮሀንስ መቀጠል አለበት” እያሉ ሲያላዝኑ የታዩበትና አሁንም ድረስ ሽንጣቸውን ገትረው የሚከራከሩበት ሚስጥሩ የሚሸጎጥላቸው ገንዘብ ነው። በነገራችን ላይ ዮሀንስ የአሜሪካ ኦሎምፒክ ቡድን አሰለጠንኩ የሚሉት ነጭ ውሸት ነው። ዮሀንስ ልጆች በወለዱላትና አሜሪካ በምትኖረው የቀድሞ የትዳር ጓደኛቸው ክስ ተመስርቶባቸዋል። የልጅ ማሳደጊያ በየወሩ መስጠት እየተገባቸው ይህን ባለማድረጋቸው ነው ክሱ። በየጊዜው እዳው እየተጠራቀመ ስለሆነ አሜሪካ የመመለስ ሀሳብ እንደሌላቸው የሚያውቋቸው ይናገራሉ።

የክሪስቲያኖ ሮናልዶ እዚህ መድረስ ሁነኛው ምስጢር‬:-

11011679_1601317420137593_1575258493282020597_n

 

ሮናልዶ እንዲህ ይላል…
“ለኔ ለዚህ ስኬት መድረስ ትልቅ አስተዋፅኦ ያደረገልኝን የልጅነት ጓደኛዬን አልበርት ፎንትራኦን አመሰግነዋለሁ! በጊዜዉ እኔና እሱ ከ18 አመት በታች ለታዳጊ ሻምፕዮና በአንድ ክለብ አብረን እንጫወት ነበር…አንድ ቀን የሊዝበን አሰልጣኝ ወደ እኛ መጣና እንዲህ አለን:- “ዛሬ ብዙ ጎል ያስቆጠረ ወደ እኛ አካዳሚ ይገባል” አለን! በእለቱም ጨዋታውን 3ለ0 ስናሸንፍ ጎሎቹንም የመጀመሪያውን እኔ 2ኛውን ደግሞ አልበርት በሚያምር የጭንቅላት ኳስ አስቆጠረ:: 3ኛዋ ጎል ግን ለኛ አጅጉን ወሳኝ ነበረች… ከዛም አልበርት እቺን ወሳኝ ጎል ለማስቆጠር ከግብ ጠባቂዉ አንድ ለ አንድ ተገናኘ በዛ ላይ እሱ ግብ ጠባቂውን አልፎ ለመሄድም ችሎታው ነበረው ግን ኳሷን ከመረብ ጋር ፈፅሞ ማገናኘትን አላሰበም እኔ ወደፊት ስሮጥ አይቶኝ ነበርና ያለቀለት ኳስ አቀበለኝ እኔም አስቆጠርኳት! ከዛም ወደ ሊዝበን የሚያስገባኝን ትኬት አገኘሁ:: ጨዋታው እንዳለቀም ወደ እሱ ሄጄ አመሰገንኩትና አንተ እኮ ማስቆጠር ትችል ነበር ግን ለምን..? ብዬ ጠየቅኩት አልበርትም “አንተ ከኔ ስለተሻልክ ነው” አለኝ::
እናም እኔ እዚህ ደረስኩ”
ታዲያ ይሄን ታሪክ በፊፋ ፎረም ያነበቡ ጋዜጠኞች የድምፅ መቅጃ ይዘው ወደ አልበርት ቤት አቀኑ…
እንዲህም ብለው ጠየቁት
‪#‎ጋዜጠኛ‬: ይሄ ታሪክ ምን ያህል እውነት ነዉ?
‪#‎አልበርት‬: በትክክል የሆነ ነገር ነዉ የዛኔ ሮናልዶን ሳየው ድንቅ እንደሚሆን አሰብኩ እኔም የ እግር ኳስ ህይወቴን የዛኔ ነዉ ያቆምኩት እንዳልተሳሳትኩም ይኸው አረጋገጠልኝ
#ጋዜጠኛ: ታዲያ አሁን በምን አይነት ስራ ላይ ነው የተሰማራኸው?
#አልበርት: ምንም ስራ የለኝም::
አዎ አልበርት ምንም ስራ የለውም ግን የሚገርም ቪላ ቤትና እየቀያየረ የሚያሽከረክራቸዉ ዘመናዊ መኪኖችና ቤተሰቡን በሙሉ በእንክብካቤ እያስተዳደረ ይኖራል::
#ጋዜጠኛ: ኑሮህ የሀብታም ነዉ ታዲያ የዚህ ሁሉ ምንጭ ከየት ነው?
#አልበርት: በኩራት ሁሉም ነገር ከክሪስቲያኖ ሮናልዶ ነዉ::
ምስሉ ላይ አልበርት ፎንትራኦና ሮናልዶ አምና በቻምፕዮንስ ሊግ ፍፃሜ ሪያል ማድሪድ አትሌቲኮ ማድሪድን 4ለ1 ባሸነፈበት ጨዋታ ሮናልዶ 4ኛውን ጎል አስቆጥሮ ሮጦ ወደ አልበርት በመሄድ ተቃቅፈው ደስታቸዉን ሲገልፁ..

አሰግድ ታመነ

የኢትዮጵያ ከ20አመት በታች የሴቶች ብሔራዊ የእግር ኳስ ቡድን በረራ ተሰርዟል ተብሎ እንዲህ ነበር የሆነው

Kalkidantube.com's photo.
Kalkidantube.com's photo.Kalkidantube.com's photo.

ኢትዮጵያዊ ስለሆንን?

(የኢትዮጵያ ከ20አመት በታች የሴቶች ብሔራዊ የእግር ኳስ ቡድን እሁድ እለት ከካሜሮን አቻው ያለግብ ከተለያየ በኋላ ወደ ሀገሩ ሊመለስ ሲል በረራ ተሰርዟል ተብሎ እንዲህ ነበር የሆነው።
ምስል፦ ኢ/ያ እ.ፌ. የህዝብ ግንኙነት ወንድኩም አላዩ)

ኢትዮጵያዊ ስለሆንን?
ቆንጅት ተሾመ
አውቃለሁ…. ሀገራቸውን ወክለው ካሜሮን የሄዱ የእንግሊዝ ብሔራዊ ቡድን ተጫዋቾች በረራ ተሰርዟል ተብሎ በአየር ማረፊያ ውስጥ በየጥጋ ጥጉ..በየመቀመጫው ..ተኮራምተው እንዲተኙ እንደማይደረግ። አውቃለሁ…የአሜሪካንብሔራዊ ቡድን ተጫዋቾች ቢሆኑ እራፊ ጨርቅ ለብሰው መሬት ላይ እንዲተኙ እንደማይደረግ።
ለስፖርት ሀገራቸውን የወከሉ የሶማሌም…የአፍጋኒስታንም …የሶሪያም ይሁን የቻይና ዜጎች ላይ እንዲህ ያለ ክብረ ነክ መጉላላት እንደማይፈጸም አስባለሁ።
እናም እጠይቃለሁ….ለምን እኛ ላይ ይህ ሆነ? ኢትዮጵያዊ ስለሆንን? ዋጋችንን ስለምን ወረደ? ለምን? ለምን? ለምን?…

posted by Aseged Tamene

የፊፋው ፕሬዝዳንት ሴፕ ብላተር ስልጣን ለቀቁ!

11109306_984622771556990_7704285237761303759_o

ለ17 ዓመታት ያህል ፊፋን በፕሬዝዳንትነት የመሩት ስዊዘርላንዳዊው ሴፕ ብላተር አሁን ስልጣናቸውን እንደሚለቁ አስታውቀዋል። በሳቸውና በተቀሩት ጓደኞቻቸው ላይ አሜሪካ የሙስና ወንጀል ፈፅመዋል በማለት ከቀናት በፊት ምርመራ መጀመሯን ተከትሎ ፊፋ እየታመሰ ነው። ደቡብ አፍሪካም የዓለም ዋንጫን በሃገሯ ለማካሄድ ለፊፋ 10ሚሊዮን ዶላር ጉቦ መስጠቷን አምናለች። አሜሪካ የወንጀል ምርመራ መክፈቷን ተከትሎ የፊፋ ዋና መስሪያቤት የሚገኝበት ስዊዘርላንድ ወንጀል መርማሪዎችም በተናጥል የራሳቸውን ምርመራ እያደረጉ ነው።

የእንግሊዝ የስፖርት ጉዳዮች ሴክሬተሪ ጆን ዊትንዴል የሴፕ ብላተርን ስልጣን የመልቀቅ ውሳኔ አስመልክቶ “እጅግ የዘገየ ውሳኔ ነው። ይህ ገና የፊፋ ሪፎርም ጅማሮ ሂደት ነው።”ብለዋል። የአውሮፓ እግር ኳስ ፌደሬሽን ፕሬዝዳንት የሆነው ሚሽል ፕላቲኒ ሴፕ ፕላተርን ይተካል ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን የሳቸውን ከስልጣን መውረድም “አስቸጋሪ፣ትክክለኛ እና ምርጥ ውሳኔ!” ብሎታል። ሴፕ ብላተር ቀጣዩ የፊፋ ፕሬዝዳንት እስከሚመረጥ ድረስ በስልጣናቸው ይቆያሉ።

የስዊዘርላንድ ጠቅላይ አቃቤ ህግ በበኩላቸው ስዊዘርላንድ ፊፋ ላይ በከፈተችው የወንጀል ምርመራ ለጊዜው ሴፕ ብላተር እንዳልተካተቱ ጠቅሰው “በምርመራችን ሂደት ውስጥ ስለሱ የምንደርስበት መጥፎ ነገር ካለ ግን ስዊዘርላንድ ውስጥ የፊፋ ፕሬዝዳንት ሆኖ አይቀጥልም።” ብለዋል።

posted by Aseged Tamene

ማሪያኖ ባሬቶ በመንግስት ጋዜጠኞች ላይ ተሳለቀ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በማሊ ብሔራዊ ቡድን መሸነፉን ተከትሎ በተዘጋጀው press conference ላይ ሐገር ቤት የሚገኙ የመንግስት እና የመንግስት ደጋፊ ጋዜጠኞች ለቡድኑ መሸነፍ አሰልጣኙን ተጠያቂ ለማድረግ የተለያዩ ጥያቄዎችን የጠየቁ ሲሆን ለጋዜጠኞቹ ምላሽ የሠጡት የብሔራዊ ቡድኑ አሰልጣኝ በጋዜጠኞቹ አቅም እና እውቀት ተሳልቀዋል፡፡
አንድ የኢቲቪ ጋዜጠኛ አሰልጣኙን “ቀኝ ተከላካይ ቦታ ችግር እያለ ለምን ሌላ ተጫዋች አልቀየሩም” ብሎ ሲጠይቅ አሰልጣኙ በግርምት “እንግዲህ ጎበዝ የቀኝ ተከላካይ እጥረት እንዳለ አውቃለው በዚህ ቦታ ጎበዝ ተጫዋች የባርሴሎናው ዳንኤል አልቬስ ነው እርሱ ደግሞ ብራዚላዊ ሆነ እንጂ ኢትዮጵያዊ ቢሆን አሰልፈው ነበር በተረፈ ደካማ ተጫዋች ለመኖሩ ተጠያቂ የሐገሪቱ አሰራር እንጂ የእኔ አሰለጣጠን አይደለም ሲሉ አክለዋል፡፡
ሌላው አስገራሚ ጉዳይ “እኛ የተሸነፍነው በማሊ ብሔራዊ ቡድን እንጂ በኦሮሚያ ብሔራዊ ቡድን አይደለም” ሲሉ ጋዜጠኞቹ ጫጫታ አሰምተዋል፡፡ አሰልጣኙ ትክክል ናቸው ምክንያቱም ለኦሮሞ ጎሳ ብሔረሠብ የሚል ስያሜ ከሠጠን ለአማራውም ጎሳ ብሔረሰብ የሚል ስያሜ ከሠጠን እና ብሔር ማለት ደግሞ የአንድ ሐገር ነዋሪ መሆኑን የሚያውቅ ጭንቅላት ካለን ለምን የኦሮሚያ ብሔራዊ ቡድን የአማራ ብሔራዊ ቡድን ሲባል ንዴት ውስጥ እንገባለን፡፡ ዘይትገርም ነው ነገሩ የመንግስት ጋዜጠኛው የብሔርን ትክክለኛ ትርጓሜ ሣያውቅ በየደቂቃው ብሔር ብሔረሠብ ሲል ይውልና የኦሮሞ የአማራ ብሔራዊ ቡድን ተብሎ ሲጠራ እምቧከረዩ ይላሉ ብሔር አለ ካላቹህ የአማራ ወይም የኦሮሞ ብሔራዊ ቡድን ሲባል ምን ያናድዳቹሀል፡፡
ትላንት እዚሁ ፌስቡክ ላይ “ብሔራዊ ቡድኑ ከተሸነፈ ለመንግስት ጋዜጠኛው ጥፋተኛ ፌዴሬሽኑና አሰልጣኙ እንጂ ፌዴሬሽኑን እና አሰልጣኙን በበላይነት የሚመራው የስፖርት ሚኒስተር አይደለም፡፡” የሚል ፅሁፍ ማስነበቤን ይታወሳል ዛሬ የመንግስት ሚዲያውን ስከታተል እንደጠበኩት አሰልጣኙን ሲሰድቡ ነው ያረፈዱት፡፡
እግር ኳሳችን እንዳያድግ እንቅፋት የሆነው የስፖርት ሚኒስቴር እንጂ አንድ አሰልጣኝ ሊሆን አይችልም አሰልጣኝ በመቀያየር ውጤት ሊመጣ አይችልም፡፡ አሰልጣኝ ከተቀየረም እንደ ገነነ መኩሪያ በእውቀት ተመርተን ሐሳብ ማቅረብ ይኖርብናል፡፡ ካልሆነ ግን ዘወትር የስፖርት ሚኒስተርን ችግር ይፋ ሳናወጣ እና እንደገነነ መኩሪያ ሊብሮ Genene Mekuria Libro የመሳሰሉትን ድንቅ ኢትዮጵያዊያን አቅም እውቀት ትተን የትም ልንደርስ አንችልም፡፡ ገነነ ብሔራዊ ቡድኑን ይመራ ዘንድ የግድ ካድሬ መሆን የለበትም፡፡

posted by Aseged Tamene