በእስር ላይ የሚገኙ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ድረሱልን እያሉ ነው

ቦረና አበራ፣ ወየቻ ታምሩ፣ ወሰኑ ገረመው፣ ዮሃንስ ፉርጋሳ፣ ገዳ ገመቹ፣ እዮብ ሙሊሳ እና ሳሎ ነጋሳ የዲላ ዩኒቨርሲቲ የኢንጅነሪንግ ትምህርታቸውን በሚከታተሉበት ወቅት ለእስር ተዳርገዋል።

የአዲስ አበባን ማስተር ፕላን ምክንያት በነበረው ሕዝባዊ ንቅናቄ ማዕከላዊ አራት ወራት ከታሰሩ በኋላ “ወንጀሉ በተፈፀመበት አካባቢ ይዳኙ” ተብሎ ሚያዝያ 28/2008 ወደ ዲላ ከተማ ተዛውረዋል። ሀምሌ 7/2008 ዓም ወደ ሀዋሳ ተዛውረው በእስር ላይ ይገኛሉ።

የካቲት 7/2010 በነበረው የፍርድ ቤት ውሎ ቦረና አበራ በነፃ ሲሰናበት፣ ቀሪዎቹ እንዲከላከሉ ተበይኖባቸዋል። ተከላከሉ ከተባሉት 6 የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች መካከል ሳሎ ነጋሳ (4ኛ አመት ተማሪ የነበረ) ብቻ “እከላከላለሁ” ሲል ወየቻ ታምሩ (የ3ኛ አመት ተማሪ)፣ ወሰኑ ገረመው (3ኛ አመት)፣ ዮሃንስ ፉርጋሳ (3ኛ አመት)፣ ገዳ ገመቹ (3ኛ አመት) “አንከላከልም” ብለዋል።

ተከሳሾቹ ከቤተሰቦቻቸው ርቀው የታሰሩ በመሆናቸው ችግር ላይ እንደሚገኙ ገልፀዋል። “የሚረዳን የለም፣ ሚዲያም እያስታወሰን አይደለም” ሲሉም ገልፀዋል።በጌታቸው ሺፈራው

 

About Aseged Tamene
Your rights are your security. When you, 'give up your rights for security", it's not security you get, but slavery.'

Leave a comment