በአዲስ አበባ ከተማ የኤች አይ ቪ ኤድስ ስርጭት በከፍተኛ መጠን እየጨመረ መምጣቱ ተነገረ

በአዲስ አበባ ከተማ የኤች አይ ቪ ኤድስ ስርጭት በከፍተኛ መጠን እየጨመረ መምጣቱንና የበሽታው ስርጭት በዚሁ ከቀጠለ ወረርሽኝ ድረጃ ሊደርስ እንደሚችል ተገለጸ።


በከተማዋ በርካታ መዝናኛዎች መስፋፋታቸው እና ጥንቃቄ የጎደለው የግብረ ስጋ ግንኙነት ለበሽታው ስርጭት ዋነኛ ምክንያት መሆኑን የአዲስ አበባ ጤና ቢሮን ዋቢ በማድረግ የመንግስት መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል።
የበሽታው ስርጭት እየጨመረ መምጣትን ተከትሎ በአዳማ ከተማ ሃገር አቀፍ ምክክር በመካሄድ ላይ ሲሆን፣ ጋምቤላና ሶማሌ ክልልም የባይረሱ ስርጭት በከፍተኛ ድረጃ እየጨመረ መሆኑ ተመልክቷል።


አዲስ አበባ ከተማን ጨምሮ በተለያዩ የሃገሪቱ ክልሎች የኤች አይ ቪ ባይረስ ስርጭት በከፍተኛ መጠን ቀንሷል ተብሎ ለረጅም ጊዜ ሲገለፅ መቆየቱ ይታወሳል።
ይሁንና በሽታው በተለይ በአዲስ አበባ ከተማ በከፍተኛ መጠን ዳግም በመሰራጨት ላይ ሲሆን፣ ስርጭቱ በዚሁ የሚቀጥል ከሆነ ወረርሽን ደረጃ ሊደርስ እንደሚችልም በመድረኩ ተገልጿል።


የጤና ጥበቃ ሚኒስትሩ ዶ/ር ወርቁ ከበደ ችግሩን ለመቅረፍ ህብረተሰቡ የህክምና አገልግሎትና ምክር የሚያገኝበት ሁኔታ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አሳስቧል።
የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር በሽታው ዳግም አሳሳቢ እየሆነ መምጣቱን ቢገልፅም የስርጭቱ መጠን ምን ደረጃ እንደደረሰና በበሽታው የተያዙ ሰዎችን ቁጥር ከመግለጽ ተቆጥቧል።


እስከቅርብ ጊዜ ድረስ በኢትዮጵያ ከሁለት ሚሊዮን በላይ የሚደርሱ ሰዎች ከቫይረሱ ጋር እንደሚኖሩ ሲገልፅ ቆይቷል።
እስከ ቅርብ አመታት ድረስ የበሽታ ስርጭቱ መጠን 2.4 በመቶ እንደነበርና በየአመቱ በ 0.29 በመቶ ይጨምር እንደነበር UNAIDS (የተባበሩት መንግስታት ድርጅት) መረጃ ያመለክታል።


ኢትዮጵያ የ HIV/AIDS ስርጭትና ሞት ከሚመዘገብባቸው የአፍሪካ ሃገራት ግንባር ቀደም መሆኗ ሲገለፅ ቆይቷል።

 

በቅማንትና አማራ ስም ህዝብ ለማፋጀት አዲስ እቅድ ወጣ!

የሰሜን ጎንደርን ህዝብ በቅማንት እና አማራ የማይገቡ ወረዳና ቀበሌዎችን በማካለል የውሸት ሪፈረደምን ተግባራዊ በማድረግ የእርስ በርስ ጦርነት እንዲያደርጉ እና እነሱም ጣልቃ በመግባት የሚፈልጉትን በግላጭ ለመግደልና ለማሰቃየት እኩይ ተግባሩን በቀላሉ ለማሳለጥ የሚያስችሉ ካድሬዎቹን አሰልጥኖ ስራ አስጀምሯል፡፡ ወያኔ የሚያደርገውን ደም አፋሳሽ አዲስና ተጨማሪ ክለላ ህዝቡ ሆን ተብሎ እንደተቀነባበረ ሊያውቅና እንደበፊት ቀደሙ በከፍተኛ ብልሃት እንዲያልፉት የሚፈጠረውን ችግር እንዲያመክን መልእክቱ በአስቸኳይ ለሁሉም እንዲዳረስ ይሁን።
ይህንን መሰሉን መሰሪ የወያኔ መርዛማ እቅድ ለማሳካት ዛሬ የሰሜን ጎንደር ዞን የፀጥታ አመራሮች ሁሉም ደባርቅ ነበሩ። የፀጥታ አመራሮች፣ የፖሊስና የልዩኃይል ኃላፊዎች አስቸኳይ ስብሰባ ማድረጋቸው ታውቋል።
ከሁለት አመት በፊት ጀምሮ ወያኔ የወልቃይት ጥያቄ በተለይ ጎልቶ ሲመጣበት በፍቅርና በአንድነት የሚኖረውን የጎንደርን ሕዝብ እርስ በእርስ ለማፋጀት የቅማንትና የአማራ በሚል ትልቅ አደጋ ማድረሱ ይታወቃል። ይህን መሰሪ ተግባር የጎንደር ህዝብ አንከፋፈልም በማለት ጠንካራ ምላሽ ቢሰጥም ወያኔ በዚህ መርዛማ ተግባሩ ሊቀጥል መወሰኑን በተደጋጋሚ መዘገባችን ይታወሳል። በቅርቡ ዋሽንግተን ዲ.ሲ. የወያኔ ኢምባሲ ለሰበሰቧቸው ካድሬወች ጎንደር ያለውን ከባድ ህዝባዊ ትግል ለማክሸፍ የአማራና የቅማንት አጀንዳን ዳግም እንደሚቀሰቅሱት መረጃው ደርሶን አጋልጠናል።
ሙሉነህ ዮሃንስ

16114034_379724762420032_2191638666481950464_n

አርባምንጭ የነጭ ሳር ፓርክ አካባቢ በተደረገው ጦርነት ከ20 ያላነሱ የመንግስት ታጣቂዎች ተገደሉ

ኢሳት ዜና :- የአካባቢው ታማኝ ምንጮች እንደገለጹት ታጣቂዎቹ ባደረሱት ድንገተኛ ጥቃት 20 የመንግስት ወታደሮች ሲገደሉ፣ በርካቶች ደግሞ ቆስለዋል። ከተገደሉት መካከል የአካባቢው ወታደራዊ አዛዥም ይገኝበታል። የተኩስ ልውውጡ ለረጅም ሰአታት የቀዬ መሆኑን የሚናገሩት ምንጮች፣ በከፍተኛ ሁኔታ የተጎዱ የመንግስት ታጣቂዎች ወደ ህክምና ተወስደዋል።
የመንግስት የጸረ ሽብር ግብረሃይል ዛሬ ባወጣው መግለጫ፣ ከኤርትራ የተንቀሳቀሱ ሃይሎች በሞያሌ በኩል ወደ አርባምንጭ ጫካ በመግባት ጥቃት ለመፈጸም ሲንቀሳቀሱ መያዛቸውን ገልጿል። መንግስት በቁጥጥር ስር የዋሉና የተገደሉ ታጣቂዎች መኖራቸውን ቢገልጽም ፣ በአሃዝ ከመግለጽ ተቆጥቧል። ይሁን እንጅ የኢሳት ምንጮች እንደገለጹት ድንገተኛ ጥቃቱን የፈጸሙት የታጠቁ ሃይሎች፣ ጥቃቱን ካደረሱ በሁዋላ ከአካባቢው ተሰውራል። ይህን ተከትሎም ከታጣቂዎች ጋር ግንኙነት አላቸው የተባሉ የከተማው ሰዎች እየታፈሱ ተወስደዋል።
አርበኞች ግንቦት 7 ጥቃቱን እንደፈጸመ በከተማው እየተወራ ቢሆንም፣ ንቅናቄው እስካሁን የሰጠው ይፋዊ መግለጫ የለም።

Gudish Weyane's photo.

በጎንደር ከተማ ከተሰማራው የፌደራል ፖሊስ ጦር ሁለት ኃይል አመራሮች ከነሙሉ ትጥቃቸው አገዛዙን ገዱ፡፡

በጎንደር ከተማ ከተሰማራው የፌደራል ፖሊስ ጦር ሁለት ኃይል አመራሮች ከነሙሉ ትጥቃቸው አገዛዙን ከዱ፡፡
አገዛዙን በመቃወም ድንገት ከጦር ሰፈር የተሰወሩት ሳጅን ጥበቡ ስብሃት እና ሳጅን አበበ ረዳይ የተሰኙ ኃይል አመራሮች ናቸው፡፡
የስማዳ ተወላጅ የሆነው ሳጅን ጥበቡ ስብሃት መጋቢት 24 2008 ዓ.ም ከነሙሉ ትጥቁ ስርዓቱን ሲከዳ አለማጣ ተወልዶ ያደገው ሳጅን አበበ ረዳይ ደግሞ ከሳምንት በኋላ ማለትም መጋቢት 30 2008 ዓ.ም የሳጅን ጥበቡ ስብሃትን ፈለግ ተከትሏል፡፡

 

በአርማጭሆ እና በሁመራ ዙሪያ የተሰማራዉን የ24ተኛ ክፍለ ጦር እየከዱ ነው

በአርማጭሆ እና በሁመራ ዙሪያ የተሰማራዉን የ24ተኛ ክፍለ ጦር እንዲያግዝ ከሸዋሮቢት ተንቀሳቀሶ በስብጥር የተዋሃደዉ የመከላከያ አብቫላት እየከዱ ወደ ጎረቤት ሐገር በመግባት ላይ ናቸዉ።
አዲስና ልምድ አልባ የሆነዉ ወጣት ወደ ግንባር እንዲሰማራ በማድረግ የጥይት ማብረጃ እያደረገዉ ነዉ የሚሉት ወገኖቻችን እጃቸዉን ለአማጺያን በመስጠትና ሾልኮ በመዉጣት የህዝብ አለኝታነታቸዉን አስመስክረዋል።
ወያኔ ከዚህ ቀደ 43ተኛ ክፍለ ጦርን ከሶማሌያ በማምጣት አዘዞ ላይ አስቀምጦት የነበረ ሲሆን ሰራዊቱ በመክዳት ምክንያት ተመናምኖ ስለነበር አፍርሶ ወደ ምስራቅ እዝ በመዉሰድ ሁለተኛ ብርጌድን ያቋቋመ መሆኑ ይታወቃል!! ያም ሆኖ የሁለጠኛ ብርጌድ ወታደራዊ አመራሮችና አስተኳሾች ባጠቃላይ በመኮብለላቸዉ ብርጌዱ እንደገና እንዲፈርስና ወደ ሌሎች እንዲጠቃለል መመሪያ መዉረዱን መረጃዎቻችን ጠቁመዋል።
ባሳለፍነዉ ሳምንት ከ24ተኛ ክፍለ ጦር ጋር የተዋጋ ሐላፊነቱን ያልወሰደ የነጻነት ሐይል ከፍተኛ ጉዳት ማድረሱን የሁመራ አካባቢ ወታደራዊ ዘመቻ ስምሪቱ ለመከላከያ አዛዙ በላከዉ መልእክት ለማወቅ ተችሏል።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!
( ጉድሽ ወያኔ )