በኢአዴግ ስራ አስፈጻሚ ስብሰባ ላይ የስራ አስፈጻሚ አባል ያልሆኑ መገኘት አነጋጋሪ ነው ተባለ

ባሁን ሰሃት የወያኔ ኢአደግ ስርሀትን ለማስቀጠል ስራ አስፈጻሚዉ ስብሰባ ላይ መጠመዳቸው ይታወቃል።
ይህ ስራ አስፈጻሚ  ነባር የሆኑትን ባሁን ሰሃት ግን ከስራ አስፈጻሚነት የተነሱት የህወሀት ባለስልጣኖችና ሌሎችም መገኘት የህወሀትን ጭንቀትና የቀድሞው ተሰሚነቱን ማጣቱ አስቆጭቶት ያንን ለመመለስ የሚያደርገው ጥረት አንዱ አካል መሆኑ ተነግራል።
ህወሀት ከገባበት አጣብቂኝ ያወጡኛል ያላቸውን በስብሰባው ላይ መገኘት የማይገባቸው እንደ በረከትና አባይ ፀዐዬ የመሳሰሉትን አስቀምጦ ውጥረት በተሞላው መልኩ ጭቅጭቁ ተጣጡፋል የተለመደው ማስፈራርያ በኦህዴድ ባለስልጣናት ላይ ይሰነዘራል ።

ህወሓቶች የመጣው ይምጣ እያሉ ያስፈራራሉ። ኦህዴድን በተደጋጋሚ ይከሳሉ። ብአዴንንም አልፎ አልፎ ያነሳሉ። በህወሃቶች ዘንድ ኦሮሚያ ውስጥ ያለውን ምስቅልቅል ሁኔታ ኦህዴድን ተጠያቂ እያደረጉ ተናግረዋል። አባይ ጸሃዬ እና ደብረጺዮን በዋናነት ኦህዴድ ላይ ጣታቸውን ቀስረዋል።

አቶ በረከት ስምዖን አሁን ጠቅላይ ሚኒስትር አያስፈልግም መጀመሪያ መከላከያ አገሪቱን ያረጋጋና ከዛ ብኋላ ይመረጣል እያለ ነው። በእሱ ስሌት መሰረት ወታደሩ እዛም እዛም የሚታዩትን ተቃውሞዎች ደብዛቸውን ካጠፋ ብኋላ ለምን ብሎ የሚጠይቅ ማንም ስለሌለ የዛንጊዜ የፈለግነው ጠቅላይ ሚኒስተር መሰየም እንችላለን ከሚል ነው፡፡

በረከት ዶ/ር አቢይ ጠቅላይ ሚኒስተር መሆን የለበትም የሚል አቋም ይዞ በስብሰባው እና ከስብሰባው በኋላ ባለው የእረፍት ጊዜ ሌሎችን ሎቢ ሲያደርግ ተስተውሏል። የተወሰኑ የህወሃት አባላት ደብረጺዮን ጠቅላይ ሚኒስተር ይሁን እያሉ ነው። ይህ የማይሆን ከሆነ ምክትሉ ከኛ ይሁን በማለት አቋማቸውን ገልጸዋል። ጌታቸው አሰፋ አሁን ደብረጺዮንን ጠቅላይ ሚኒስተር ማድረግ አሁን ካለው የፖለቲካ ሁኔታ አንጻር ፈጽሞ መሆን የሌለበት ነው በማለት አቋሙን ገልጿል። በህወሃት መካከል ቀጣይ ማን ጠቅላይ ሚኒስተር ይሁን በሚለው ጉዳይ ላይ ሙሉ በሙሉ አንድ አይነት አቋም እንደሌለ ታይቷል::

እስካሁን ያለውን የሃገሪቱ ሁኔታም እየገመገሙ ነው፡፡ በረከተ በስብሰባው ላይ ዋና ተዋናይ ሆኗል።ስብሰባው እንደቀጠለ ነው።

 

ከፍተኛ የኦሮሚያ ጦር አዛዦች ከሃላፊነታቸው እየተነሱ ነው ተባለ

በኦሮሚያ የተቀሰቀሰውን ተቃውሞ ተከትሎ መከላከያ ውስጥ የሚገኙ ከፍተኛ ኦሮሞ የሆኑ የጦር አዛዦች ቀጥታ ሰራዊቱን ከሚያዙበት ምድቦች እየተነሱ ምንም ስራ በሌለባቸው ቦታዎች እየተመደቡ እንደሆነ ታውቋል።

በኦሮሚያ ክልል የተነሳውን ተቃውሞ ተከትሎ ኦሮሞ የሆኑ የሰራዊቱ ከፍተኛ መኮንኖች ተቃውሞውን ይደግፋሉ የሚል ምልከታ በህወሃት የጦር አዛዦች መያዙን ለመረዳት ተችሏል። ታችኛው ላይ ያለው አብዛኛው ሰራዊት ከሌላ ብሄር የመጡ በመሆናቸው እነዚህ የኦሮሞ ከፍተኛ መኮንንኖች ኦሮሚያ ውስጥ የተቀሰቀሰውን ተቃውሞ ምክንያት አድርገው ታች ላይ ያለውን ሰራዊት በማንቀሳቀስ ህወሃት ላይ አደጋ እንዳያመጡና የተቃውሞው አካል እንዳይሆኑ በማለት ቀጥታ ሰራዊት ማዘዝ የማይችሉባቸው ቦታዎች ላይ እንዲመደቡ ተደርጓል።

በዚህ መሰረት የ24ኛ ክ/ጦር ዋና አዛዥ የነበሩት ብ/ጄነራል ሹማ አብደታ ከሃላፊነታቸው ተነስተው በሹመት ስም ምንም ጦር ማዘዝ በማይችሉበት ቦታ በሆነው የደቡብ ምስራቅ እዝ ም/ል አዛዥና የሰው ሃብት ልማት ሃላፊ በማለት እንዲመደቡ ተደርገዋል።

በብ/ጄነራል ሹማ አብደታ ምትክ የ24ኛ ክ/ጦር ዋና አዛዥ በመሆን ኮ/ል የማነ ገ/ሚካኤል የተባሉ የህወሃት የጦር አዛዥ ተመድበዋል። የ13ኛ ክ/ጦር ዋና አዛዥ የሆኑት ብ/ጄነራል ከድር አራርሳ ቀጥታ ጦሩን ከሚያዙበት ሃላፊነታቸው እንዲነሱ ተደርጎ በሹመት ስም ምንም ጦር ወደ ማይመሩበትየማዕከላዊ እዝ ም/ል አዛዥና የሰው ሃብት ልማት ሃላፊ በመሆን ተመድበዋል።

የ6ኛ ሜካናይዝድ ክ/ጦር ዋና አዛዥ የሆኑት ብ/ጄነራል ከፍያለው አምዴ እንዲሁ ከሃላፊነታቸው እንዲነሱ ተደርጓል። የ21ኛ ክ/ጦር ዋና አዛዥ የሆኑት ብ/ጄነራል ዋኘው አማረ ከሃላፊነታቸው ተነስተው በመሃንዲስ ዋና መምሪያ ውስጥ እንዲቀመጡ ተደርጓል።

የአጋዚ ኮማንዶና ልዩ ሃይሎች ጠቅላይ መምሪያ ም/ል አዛዥና የኦፕሬሽን ሃላፊ የሆኑት ብ/ጄነራል ሙላት ጀልዱ ከላፊነታቸው ተነስተው በመከላከያ የስነምግባር መከታተያ ዳይሬክተር በማድረግ ከሰራዊቱ ጋር ቀጥታ ከሚያገናኛቸው ስራዎች እንዲገለሉ ተደርጓል።

በርካታ የአማራና የኦሮሞ ከፍተኛ መኮንኖች በሰላም ማስከበር ሰበብ ከሰራዊቱ እንዲገለሉ የማድረግ ስራዎች እየተሰሩ እንደሆነ መከላከያ ውስጥ ያሉ ምንጮቻችን ገልጸዋል። በኦሮሚያ ክልል የተነሳውን ተቃውሞ ተከትሎ ሰራዊቱ ተቃውሞውን እንዳይቀላቀል በህወሃት በኩል ከፍተኛ ስራዎች እየተሰሩ ያሉ ሲሆን ለህዝብ ወገኝተኝነት ያሳያሉ የሚባሉ የጦር አዛዦችን ከሃላፊነታቸው በማንሳት ምንም ወደ ማይሰሩበት ቦታዎች በሹመት ስም እየተዛወሩ መሆኑ ታውቋል።

ከአዲስ አበባ ወደ ጎጃም መስመር ትራንስፖርት መቆሙ ተነገረ

ከሰሜን ሸዋ በሙከጡሪ ከተማ ተገንጥሎ ያሉት ቆላማወች ለሚ እና መርሃቤቴ ከተሞች ፣ በጎጃም ደጀን ሉማሜ ከተሞች ህዝባዊ አመፁ ሞቅታ እየደረሳቸው መሆኑ ተነገረ።

ከአ.አ በቅርብ ርቀት ከሱሉልታ እስከ ጉሃፅዩን ድረስ የአባይን ድልድይ ሳይሻገሩ የተቀጣጠለው ህዝባዊ አመፅ ና ቁጣ ወደ ጎጃምና ሰሜን ሸዋ እንዳይዛመት በመስጋት የወያኔ አጋዚ ጦር እየሰፈረ ይገኛል።

የትራንስፖርት አገልግሎት ሙሉ ለሙሉ በሚባል መልኩ መቆሙም የተነገረ ሲሆን
በህዝባዊ አመፁ በወያኔ የአጋዚ ወታደሮች የሀይል እርምጃ የተቆጣው ህዝብ በወሰደው እርምጃ በርካታ ተሽከርካሪወች ና ቤቶች መቃጠላቸውን ተከትሎ ከአባይ በረሃ ተሻግሮ ባሉት ከተሞች በርካታ ተሽከርካሪወች በመንገዱ ግራናቀኝ ተሰትረው ይገኛሉ።

ከትራንስፖርት መስተጓጎሉ ባሻገር ከግብር ጋር ተያይዞ በክረምቱ ህዝባዊ አድማ ሲደረግባቸው የነበሩ ከተሞች በመሆናቸው የኦሮሚያው ህዝባዊ አመፅ ሞቅታው ስለደረሳቸው ህዝቡ ለአመፅ እንዳይነሳ በከተሞቹ ካድሬወች ተሰግቷል።


በደጀን ከተማ በርካታ ተሽከርካሪወች የቆሙ ሲሆን ከጎንደር አ.አ እና ከጎጃም አዲስ አበባ የሚደረጉ ጉዞወች ተሰርዘዋል። በተለይ የህወሓት ንብረት የሆኑና ከሥርዓቱ ጋር የቅርብ ግንኙነት የጥቅም ተቋዳሾች ትልልቅ ልዩ አውቶብሶች የጉዞ ትኬታቸውን ለትናንት የተቆረጠ የመለሱ ሲሆን ዛሬ ጉዞ እንደማያደርጉ ገልፀው ትኬት ከመሸጥ ተቆጥበው ውለዋል።


ከመከጡሪ ከተማ በስተቀኝ ተገንጥሎ 50 ኪ.ሜ ርቀት ላይ ለሚ ከተማ እንዲሁም ከ100 ኪ.ሜ ርቀት ላይ የሚገኘው መርሀቤቴ አጠቃላይ ቆላው ዙሪያ ገባው በአብዛኛው በመከጡሪ ከተማ በነበረው ህዝባዊ አመፅ ተሳታፊ የነበረ ሲሆን ወደ ከተሞቹ የትራንስፖርት እንቅስቃሴ ቆሞ ውሏል። ከተሞቹ እንደሌሎቹ የኦሮሚያ ከተሞች ጭር ብለው በወያኔ ወታደሮች ተወረው ውለዋል።


በተያያዘ መረጃ ከአባይ በረሃ ተሻግረው ባሉ ዙሪያው አካባቢ ባሉ ጥቃቅን መንደሮች የወያኔ ወታደሮች አፈሳ ሲያደርጉ እንደነበር ተሰምቷል።

የወያኔ ስርሀት የመጨረሻው ጫፍ ላይ የደረሰ ይመስላል ተባብረን እንግፋው

የህወሓትን አምባገነን ስርዓት በመክዳት የሚጠፉት ወታደሮች ቁጥር ጨምሯል።

በሰሜን ዕዝ 25ኛ ክ/ጦር አባላት በቡሬ ግምባር እና በማንዳ አካባቢ ካሉ የመከላከያ አባላት ስርዓቱን በመክዳት እየጠፉ በተለያዩ የሀገራችን ክፍሎች ከህዝቡ ጋር ተቀላቅለው ገብተዋል። የህወሓት ወታደራዊ አዛዦች ታማኝ ቅጥረኞች የጠፉትን ለመፈለግ ወደ ተለያዩ ከተሞች በውሎ አበል ወጥተዋል።
ትግሬ ወያኔ ካልሆኑ በስተቀር በተለይ ለአማራ እና ለኦሮሞ ተወላጆች የአመት ዕረፍት እና ቤተሰብ ጥየቃ የማይፈቀድበት የሰሜን ዕዝ ቡሬ ግምባር ስርዓቱን በመክዳት በተለያዩ መንገዶች ወደ ታጋይ አርበኞች ለመቀላቀል ያልቻሉ እራሳቸውን በመሰወር ላይ ሲሆን የስርዓቱ ወታደራዊ ጀነራሎች ከፍተኛ መቃወስ ውስጥ ገብተዋል።በቤተሰብ ወዳጂ ዘመድ ጉትጎታ እና ስርዓቱ እያደረሰው ባለው ጭቆናና ግፍ ተማረው 6 የአማራ ተወላጆች በተለያየ ቀን ተከፋፍሎ በሳምንት ውስጥ ከቡሬ ግምባር ለማምለጥ ችለዋል። ከኢትዩ-ኤርትራ -ጂቡቲ ድንበር አሊ ሙሳ ተራራ ጀምሮ በተመደቡበት ሁሉ በከፍተኛ ምሬት ውስጥ የሚገኙት የመከላከያ አባላት በስርዓቱ የሚደርስባቸው በደል ግፍ መጀመሪያም አማራጭ አጠን የገባንበትን ወታደራዊ ሙያ እጂጉን እንዲያስጠላን አድርጓል ይላሉ። በወያኔ ወታደራዊ አዛዦች የሚደርስብን በደል ለስርዓቱ የስልጣን ወንበር ጠባቂ አድርጎን በጥይት አረር ውስጥ እየጣደን እስከመቼ በዝምታ እንመልከት በማለት ከህዝባቸው ጋር ለመታገል መወሰናቸውን ተናግረዋል ። ለምግብ(ሬሽን ) በየወሩ ከ350 ብር እስከ 400 ብር ከተራው ወታደር እየተቆረጠብን ፣ ወደ ኪሱ የሚገባው ከ700 ብር በታች ነው። በዚህም ላይ በየአራት ወሩ ደሞዝ አይሰጥም ይህም ለወታደታዊ ልብስ(ሬንጀር ) ፣ቲሸርት ፣ጫማ ወዘተ ተብሎ ይወሰዳል ። በተለያየ ጊዜም በወታደራዊ ትግሬ አዛዦች ውሳኔ ብቻ ያለእኛ ፈቃድ ለመለስ ፖርክ ፣ፍውንዴሽን እየተባለ በአክሱም አካባቢ ት/ቤት ለማሰራት እየተባለ ፣መሰል ምክንያቶችን ደርድረው ከ700 ብር በታች ከምግብ ተቀንሳ የምትደርሰንን ደሞዝ ቆራርጠው ይወስዱታል በማለት በምሬት ይናገራሉ።
በአብዛኛው ወታደሮች ጠፍተው ለመውጣት ሱና ፣ ሪዳር፣ ዲሽቶ፣ ሚሊ የመሳሰሉ ኬላወችን ለማለፍ ከ13 ሺ እስከ 16ሺ ብር በአሽከርካሪወች ይጠየቃሉ ይሄም እድል ካለ ነው። ከዚህ ላይ እድል ሁኖ በኬላወቹ የተያዘ ፣ እንዲሁም ለማደን በሚወጡ ታማኝ ቅጥረኞች ተይዞ ወደ ካምፕ የሄደ ለመላ ወታደሮች እስር እንደተፈረደበት ለመቀጣጫ ይነገር እና ከተወሰነ ጊዜ የስቃይ እስር በኋላ ተባሯል ይባላል። ይህም ማለት ተረሽኗል ማለት ነው።
ብዛት ያላቸው ወታደሮች ወደ ተለያዩ አቅጣጫወች ሲጠፉ የተያዙ እና ተስፋ ቆርጠው በየካምፑ እስር ቤቱ የነበሩ ወታደሮች በአብዛኛው የት እንዳሉ አይታወቅም። ብዛት ያላቸው ወታደሮች ግን በስርዓቱ በመማረር በዚህ 2 ሳምንት ውስጥ ጠፍተዋል ፤አሁንም ጠፍተው ለመውጣት ብዙወቹ ቆርጠው ምቹ ሁኔታን ይጠባበቃሉ።ከእጃቸው የምትገባ ትንሽ ብርም በምሬት በየካምፑ አቅራቢያ በሚገኙ ትንንሽ መንደሮች በሲጋራ እና ጫት ሱስ ተጋልጠዋል።

በሙስና ወንጀል የተጠረጠሩ የመንግሥት ኃላፊዎችና ባለሀብቶች ቁጥር 53 ደረሰ

ከ1.3 ቢሊዮን ብር በላይ በሕዝብና በመንግሥት ሀብት ላይ ጉዳት በማድረስ የተጠረጠሩት የገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ዓለማየሁ ጉጆ፣ የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣን የቀድሞ ዋና ዳይሬክተር አቶ ዛይድ ወልደ ገብርኤል፣ በስኳር ኮርፖሬሽን የመስኖና ቤቶች ልማት ፕሮጀክት ልማት ዘርፍ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ኪሮስ ደስታና ሀዚ አይ አይ ደረጃ አንድ ጠቅላላ ተቋራጭ ባለቤት አቶ ዛኪር መሐመድ ናቸው፡፡

የፌዴራል ፖሊስ መርማሪ ቡድን እያንዳንዱ ተጠርጣሪ ምን ያህል በሕዝብና በመንግሥት ላይ ጉዳት እንዳደረሰ፣ ለፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ሁለተኛ ወንጀል ችሎት አስረድቷል፡፡

አቶ ዓለማየሁ ጉጆ የገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ሚኒስቴር አሠራሩን ዘመናዊ ለማድረግ የሚያዘረጋውን ቴክኖሎጂ መመርያንና ደንብን መሠረት ያደረገ ዓለም አቀፍ ጨረታ ማውጣት ሲገባቸው፣ ለማይታወቅና በቂ ልምድ ለሌለው ድርጅት በመስጠት ከ2.2 ሚሊዮን ዶላር በላይ ጉዳት እንዲደርስ ማድረጋቸውን መርማሪ ቡድኑ አስረድቷል፡፡ በተጨማሪም መከፈል ያልነበረበትን 280,000 ብር ሲፒኦ በማሠራት ክፍያ እንዲፈጸም በማድረግ ሥልጣናቸውን በመጠቀም፣ የመንግሥትን ሥራ በማያመች አኳኋን መምራታቸውንም አክሏል፡፡ በፍርድ ቤቱ ያቀረበው የምርመራ ሒደት መነሻ እንጂ ሙሉ ምርመራ አለማድረጉን የገለጸው መርማሪ ቡድኑ፣ ለቀሪ የምርመራ ጊዜ 14 ቀናት እንዲፈቀድለት ጠይቋል፡፡

አቶ ዓለማየሁ በሰጡት ምላሽ እንደተናገሩት፣ በተጠረጠሩበት ጉዳይ የተደራጀ መረጃ በመሥሪያ ቤቱ ይገኛል፡፡ በእሳቸው ግምት እስከተያዙበት ባለው ጊዜ ውስጥ መርማሪ ቡድኑ ምርመራውን እያጠናቀቀ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ የስኳር ሕመምተኛ መሆናቸውን ለፍርድ ቤቱ ገልጸው፣ ታስረው የሚገኙበት ክፍል ውስጥ 20 ሰዎች በመኖራቸው መንቀሳቀስ እንደማይችሉ ጠቁመዋል፡፡ የስኳራቸው መጠን በከፍተኛ ሁኔታ በመጨመሩ አሥጊ ሁኔታ ላይ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ ከተያዙ ቀን ጀምሮ ቤተሰቦቻቸውንም ሆነ ማንንም ሰው ማግኘት ባለመቻላቸው፣ በቂና አስተማማኝ ዋስ ጠርተው ጉዳያቸውን በውጭ ሆነው እንዲከታተሉ ፍርድ ቤቱን ጠይቀዋል፡፡

አቶ ዛይድ ወልደ ገብርኤልን በሚመለከት መርማሪ ቡድኑ ለፍርድ ቤቱ እንደገለጸው፣ ለተለያዩ ተቋራጮች የተሰጡ አምስት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቶች ጥራታቸውን ያልጠበቁ ዲዛይኖችን በማሠራት፣ የኮንትራት ጊዜያቸውን ባለመጥቀስ፣ የግንባታ ጊዜ በማራዘምና ከኮንትራክተሮች ጋር በመመሳጠር በሕዝብና በመንግሥት ላይ ከአንድ ቢሊዮን ብር በላይ ጉዳት ማድረሳቸውን አስረድቶ፣ ለተጨማሪ ምርመራ 14 ቀናትን ጠይቋል፡፡

አቶ ዛይድ በጠበቃቸው በኩል ለፍርድ ቤቱ እንደገለጹት፣ መርማሪ ቡድኑ የገለጸው በሰነድ የሚታይ በመሆኑ የጠየቀው 14 ቀናት ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ተገቢ አይደለም፡፡ አቶ ዛይድ ባለሥልጣኑን ከለቀቁ ሁለት ዓመት እንዳለፋቸውና መንግሥት ከአገር ውጭ ለሥራ መድቧቸው እየሠሩ መሆናቸውን ጠበቃው አስረድተዋል፡፡

የስኳር ኮርፖሬሽኑ አቶ ኪሮስ ደስታ ደግሞ የመስኖና ቤቶች ልማት ፕሮጀክት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ሆነው ሲሠሩ፣ ለጣና በለስ ፕሮጀክት ቧንቧ ግዥ በጨረታ ከቀረበው ዋጋ በላይ ለሦስት ጊዜያት 2,983,396 ብር፣ 131,554,000 ብር እና 49,559,992 ብር ግዢ እንዲፈጸም ማድረጋቸው ተገልጿል፡፡ ለየማነ ግርማይ ጠቅላላ ኮንስትራክሽን ድርጅት 20 ሚሊዮን ብር የሚገመት ንብረት በመስጠት በሕዝብና በመንግሥት ላይ ጉዳት ማድረሳቸውንና የመንግሥትን ሥራ በማያመች አኳኋን መምራታቸውን ለፍርድ ቤቱ አስረድቷል፡፡

አቶ ኪሮስ በሰጡት ምላሽ ድርጅቱን ከለቀቁ ሁለት ዓመት እንዳለፋቸው ተናግረዋል፡፡ ከቤታቸውም ሆነ ከመሥሪያ ቤቱ ሁሉም ዶክመንቶች የተወሰዱ መሆኑን በመግለጽ፣ ተጨማሪ 14 ቀናት የምርመራ ጊዜ መጠየቅ ተገቢ አይደለም ሲሉም ተቃውመዋል፡፡

ልጃቸው ዩኒቨርሲቲ ስለምትገባ በስልክ አግኝተው እንዲያነጋግሯት ፍርድ ቤቱ ትዕዛዝ እንዲሰጥላቸውም ጠይቀዋል፡፡ ቀደም ብሎ በተጠረጠሩበት የሙስና ወንጀል በቁጥጥር ሥር ውለው በታሰሩት እነ ካሣይ ካቻ መዝገብ የተካተቱት የሀዚ አይ አይ ደረጃ አንድ ሥራ ተቋራጭ ባለቤት አቶ ዛኪር መሐመድ ግምቱ 3,315,200 ብር የሆነ 500 በርሜል አስፋልት በውሰት ወስደው አለመመለሳቸውን መርማሪ ቡድኑ ለፍርድ ቤቱ አስረድቷል፡፡ አቶ ዛኪር በሁለት ወራት ውስጥ ለመመለስ የተዋሱትን አስፋልት፣ ከኃላፊዎች ጋር በመመሳጠር ሳይመልሱ መቅረታቸውንና ከላይ የተጠቀሰውን የገንዘብ መጠን ያህል ጉዳት ማድረሳቸውን አስረድቷል፡፡

አቶ ዛኪር በሰጡት ምላሽ መርማሪ ቡድኑ የገለጸውን ዕዳ መክፈላቸውን ገልጸው፣ ተጨማሪ 14 ቀናት ሊፈቀድ አይገባም ብለዋል፡፡ የዋስትና መብታቸውም እንዲከበርላቸው ጠይቀዋል፡፡

ፍርድ ቤቱ ክርክሩን ከሰማ በኋላ በሰጠው ትዕዛዝ የሁሉንም ተጠርጣሪዎች የዋስትና ጥያቄ ውድቅ አድርጓል፡፡ አቶ ዛኪር ቀደም ብለው ፍርድ ቤት ከቀረቡት ጋር ነሐሴ 11 ቀን 2009 ዓ.ም. እንዲቀርቡ በማለት የአሥር ቀናት ጊዜ ፈቅዷል፡፡ በአቶ ዓለማየሁ፣ በአቶ ኪሮስና በአቶ ዛይድ ላይ የቀረበውን የ14 ቀናት ጊዜ በመፍቀድ ነሐሴ 15 ቀን 2009 ዓ.ም. እንዲቀርቡ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡

ተጠርጣሪዎቹ በቤተሰብ፣ በሕግ ባለሙያና በሃይማኖት አባት የመጎብኘት ሕገ መንግሥታዊ መብት እንዳላቸው ፍርድ ቤቱ ገልጾ፣ የፌዴራል ፖሊስ ትዕዛዙን ተግባራዊ እንዲያደርግ አሳስቧል፡፡ ሕክምናን በሚመለከትም ከመንግሥት የሕክምና ቦታዎች በተጨማሪ፣ የሚፈልጉትን ሕክምና እንዲያገኙም እንዲያደርግ ትዕዛዝ ሰጥቷል፡