በአየር ሃይል አውሮፕላን ጥቃት ተሰዘነረ

90 የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት አባላትን የጫነ የአየር ሃይል አንቶኖቭ አውሮፕላን ከመጋየት መትረፉን የቅርብ ምንጮች ያደረሱኝ መረጃ ያመለክታል። ዛሬ ጠዋት ከረፋዱ 4፡00 ሰዓት አቆጣጠር 90 የኢትዮጵያ የሰላም አስከባሪዎችን አሳፍሮ ደቡብ ሱዳን – ሃዲጉሊ የተባለች ግዛት የደረሰው አንቶንቭ አውሮላን ወደ መሬት እየወረደ ባለበት ወቅት ማንነታቸው ባልታወቁ ታጣቂዎች በዲሽቃ በተተኮሰ ሁለት ጥይት በጎን በኩል እንደተመታ ምንጮቹ ጠቁመዋል። በአብራሪዎቹና ወታደሮቹ ድንጋጤ ተፈጥሮ እንደነበረ ያመለከቱት ምንጮቹ የተተኮሰው ጥይት ሞተሩ አካባቢ ቢያርፍ ኖሮ አውሮፕላኑ ሊነድ ይችል እንደነበረ አስታውቀዋል። አንቶኖቭ አውሮፕላኑ ባላፈው ሳምንት በአንዱ የሞተር ክፍል ብልሽት ገጥሞት ለሰባት ቀናት በጥገና ላይ እንደሰነበተ ምንጮቹ አስታውቀዋል። በደቡብ ሱዳን በየጊዜው ከሚሰማራው የመከላከያ ሰራዊትና ሰላም አስከባሪ ሃይል የመከላከያ ጄኔራሎች በሚሊዮን የሚቆጠር ዶላር ከሰራዊቱ እየዘረፉ ኪሳቸው እንደሚያስገቡ የሚታወቅ ሲሆን ዝርዝር መረጃውን በቅርቡ የምንመለስበት ይሆናል።

አርአያ ተስፋማሪያም

posted by Aseged Tamene

About Aseged Tamene
Your rights are your security. When you, 'give up your rights for security", it's not security you get, but slavery.'

Leave a comment