የነጻነት ተጋድሎው በሰሜን ጎንደር ተጠናክሮ ቀጥሏል፥
November 14, 2016 1 Comment
አሻፈረኝ ብለው ከወያኔ ሰራዊት ጋር ለመፋለም ጫካ የከተቱ ታጣቂዎች፥ ታች አርማጭሆ ሳንጃ የወያኔ የጦር ካምፕ ላይ ጥቃት አድርሰው የወያኔ ወታደሮችን መግደላቸው ተሰምቷል::
ታጣቂዎች ቅዳሜ ሌሊት ሳንጃ የሚገኘው የትግራይ ነጻ አውጪ ግንባር ወታደራዊ ካምፕ ላይ አደጋ ጥለው የጦሩን አዛዥ ጨምሮ 4 ወታደሮችን ገድለዋል፥ በተወሰደው እርምጃ በርካታ የጦር መሳሪያዎችን መማረካቸውም ታውቋል።
ሳንጃ ላይ ሌሊሉትን የዘለቀ ከፍተኛ ውጊያ ሲደረግ ማደሩና በተሳካ ሁኔታ ግዳያቸውን ጥለው፥ የወታደርና የትጥቅ ምሮኮ ቀንቷቸው በድል መሰወራቸው ታውቋል።
ከዚህ ጋር ተያይዞ፥ አርማጭሆ ዋሊያ ቀበሌም እንደዚሁ የወያኔ ኮማንድ ፖስት ማዘዣ ጣቢያ ላይ ታጣቂዎች አደጋ ጥለው የወያኔ ወታደሮች ላይ የደረሰ ጉዳይ ባይታወቅም ነፍሴን ዓውጭኝ ብለው እንዳመለጡና ካምፑ ሙሉ በሙሉ መቃጠሉ ተሰምቷል፥
ጎንደር ተማምሏል፥ ከወያኔ ጋር እንዲህ በዋዛ አንላቀቅም ብሏል አገሬ።
ሰሜን አርማጭሆ ወልቃይት ጠገዴ፥ የእነ ካሳሁን አበራ አገር፥ የእነ ፍርዱ ልዩነህ የእነ አበራ ጎባው መንደር አርማጭሆ፥ የጀግናው ኪዳነ ማሪያም አገር እንቃሽ፥ አጅሬ ጇኗራ በእግራና በቀኛ ጠምዶ ወያኔን እያረሰው ነው።
ሞት ለወያኔ፥ ድል ለሰፊው ሕዝብ፥
Yashewan(2) Gena (2)
. .
Mech Tewagana .
LikeLike