በሀዲያ ዞን ሆሳዕና ከተማ የከተማ ታክሲዎችን ጨምሮ የህዝብ ማመላለሺያ ተሽከርካሪዎች ከትላንት ጀምሮ የስራ ማቆም አድማ አደረጉ
January 19, 2016 1 Comment
ዜና ከደቡብ ኢትዮጵያ
በሀዲያ ዞን ሆሳዕና ከተማ የከተማ ታክሲዎችን ጨምሮ የህዝብ ማመላለሺያ ተሽከርካሪዎች ከትላንት ጀምሮ የስራ ማቆም አድማ አድርገዋል። መንግስት በአሽከርካሪዎች ላይ ያወጣው አዲስ መመሪያን ተከትሎ በተነሳ ቁጣ አሽከርካሪዎችና ባለንብረቶች የስራ ማቆም አድማ መምታቸውን ለኢሳት ከአከባቢው የደረሰው መረጃ አመልክቷል። ከትላንት ጀምሮ ምንም አይነት የህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪ ከሆሳዕና መግባትም መውጣትም እንዳልቻለ በአድማው የተሳተፈ አንድ አሽከርካሪ ገልጿል። ከወራቤ ወደ ሆሳዕና 16 ሰዎችን ጭኖ ሲያመራ የነበረ መለስተኛ የህዝብ ማመላሺያ ተሽከርካሪ በአድመኞቹ ጥቃት ተሰንዝሮበት እንደወደመ ያገኘነው መረጃ ያመልክታል። አድማውን ህዝቡ እየተቀላቀለው እንደሆነ ተገልጿል። ለነገ ሰላማዊ ሰልፍ መጠራቱንም ለማወቅ ተችሏል።
Reblogged this on First Ethiopia.
LikeLike