የግብጽ ኦርቶዶክስ ክርስቲያኖች በአውቶብስ ተሳፍረው በጉዞ ላይ እንዳሉ ጭምብል ባጠለቁ ሰዎች ጥቃት ደረሰባቸው
May 26, 2017 Leave a comment
የግብጽ ኦርቶዶክሶች ዛሬ በማለዳ 240 ኪ.ሜ ከካይሮ በስተደቡብ ወደሚገኘው ወዳ ጻድቁ አባ ሳሙኤል ገዳም በአውቶብስ ተሳፍረው በጉዞ ላይ እንዳሉ ጭምብል ባጠለቁ የወታደር ልብስ የለበሱ አስር ታጣቂዎች በተከፈተባቸው ቱኩስ አውቶብሱ ሲቃጠል 26 ክርስቲያኖች ወዲያው ሲሞቱ 25ቱ በጽኑ መቁሰላቸውን እና በአስጊ ሁኔታዎች ላይ ናቸው ሲል ቢቢሲ፣ሲኤን ኤን ዘግበውታል።እስከ አሁን ኅላፊነቱን የወሰደ አካል ባይኖርም አሸባሪዎች እንደሚሆኑም ተገምታል። ከሞቱትም መካከል ሴቶችና ህጻናት ይገኙበታል።