ህወሓት ሶስት አባላት ያሉት ልዑክ እነ ጅዋር መሀመድን ለማነጋገር ወደ ዋሽንግተን ልትልክ ነው”
January 1, 2016 Leave a comment
የልዑኩ አባላት በአባ ዱላ ገመዳ ጠቛሚነት ተመርጠው የተዋቀሩ ሆድ አደር የኦህዴድ ካድሬዎች ሲሆኑ ሁለቱ በአዲስ አበባ ዪኒቨርስቲ በመምህርነት ያገለግላሉ። የጉዞ አላማቸው ለነ ጅዋር መሀመድ ማስተር ፕላኑን በተመለከተ ማብራርያ መስጠትና እነ ጅዋር የሚቃወሙት ነገር ካለ እንደሚቀር ማረጋገጫ መስጠት ነው ተብሎአል። እንደምንጮቸ ከሆነ ጅዋር የቀረበለትን ጥሪ ከወዲሁ ውድቅ አድርጎታል። ሰዎቹ ግን ዛሪ ማታ ከምሽቱ አራት ሰአት ላይ ከቦሌ አለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ይነሳሉ ከግርማ ብሩ ጋር በመሆንም እነ ጅዋርን ለማግኘት ከፍተኛ ጥረት ያደርጋሉ።