የፌደራል ጉዳዮች ሚኒስቴር ከቤንሻንጉል ጉሙዝ የተፈናቀሉት ዜጎች ለክስ የሚያበቃ በደል አልደረሰባቸውም አለ።

የፌደራል ጉዳዮች ሚኒስቴር ከቤንሻንጉል ጉሙዝ የተፈናቀሉት ዜጎች ለክስ የሚያበቃ በደል አልደረሰባቸውም አለ።

ኢሳት ዜና ፦ ከቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልል የተፈናቀሉ ዜጎች በተወካዮቻቸው አማካኝነት የመሰረቱት ክስ በፌደራል ከፍተኛው ፍርድ ቤት 8ኛ ፍትሃ ብሄር ምድብ በዋለው ችሎት የታየ ሲሆን ፣ በቀረበው ክስ ላይ የፌደራል ጉዳዮች ሚኒስቴርና የቤንሻንጉል ክልል መንግስት መልስ ሰጥተዋል።

ከሳሾች ለበርካታ አመታት ከኖሩበት ቀየ በህገወጥ መንገድ በመፈናቀላቸው ሃብትና ንብረታቸውን ማጣታቸውን በጠበቃቸው አማካኝነት ተናግረዋል። የፌደራል ጉዳዮች ሚኒስቴር በበኩሉ ከሳሾቹ ቤት ንብረት አለማፍራታቸውን ጠቅሶ፣ ምንም ለክስ የሚያበቃ ነገር ሳይኖራቸው ጉዳያቸው ለፖለቲካ ፍጆታነት እየዋለ ነው በማለት መልስ ሰጥቷል።

በጉዳዩ ዙሪያ ላይ ያነጋገርናቸው ጠበቃው ዶ/ር ያዕቆብ ሃይለማርያም የፌደራል ጉዳዮች ሚኒስቴር «ጉዳዩ የሚመለከተው የክልሉን መንግስት እንጅ የፌደራሉን አይደለም» በማለት የሰጠው መልስ ትክክል አለመሆኑን ተናግረዋል። የህገመንግስቱ አንቀጽ 52 ማንኛውም የሰብአዊ መብት ጥሰት ሲፈጸም የፌደራል መንግስቱን እንደሚያገባው፣ በዚህም የተነሳ የፌደራል መንግስቱ አይመለከተኝም ማለት እንደማይችል ገልጸዋል።

ዶ/ር ያዕቆብ ጠ/ሚ ሃይለማርያም ደሳለኝ «ከቤንሻንጉል ጉሙዝ ሰዎች እንዲፈናቀሉ ያደረጉትን ለፍርድ እናቀርባለን» በማለት ተናግረው እንደነበር አስታውሰዋል። አሁን እየታየ ያለው ግን የዚህ ተቃራኒ ነው ነው ሲሉ አክለዋል።

posted by Aseged Tamene

 

About Aseged Tamene
Your rights are your security. When you, 'give up your rights for security", it's not security you get, but slavery.'

2 Responses to የፌደራል ጉዳዮች ሚኒስቴር ከቤንሻንጉል ጉሙዝ የተፈናቀሉት ዜጎች ለክስ የሚያበቃ በደል አልደረሰባቸውም አለ።

  1. Pingback: የፌደራል ጉዳዮች ሚኒስቴር ከቤንሻንጉል ጉሙዝ የተፈናቀሉት ዜጎች ለክስ የሚያበቃ በደል አልደረሰባቸውም አለ። | One Democratic Ethiopia

  2. Pingback: የፌደራል ጉዳዮች ሚኒስቴር ከቤንሻንጉል ጉሙዝ የተፈናቀሉት ዜጎች ለክስ የሚያበቃ በደል አልደረሰባቸውም አለ። - EthioExplorer.com | EthioExplorer.com

Leave a comment