ሩሲያ የሶሪያን የአየር ጥቃት የመከላከል አቅም እንደምታጠናክርና እንደምታሳድግ አሳወቀች
April 7, 2017 Leave a comment
ትራምፕ ሀገራቸው በሶሪያ ላይ የምትወስደውን እርምጃ አጠናክራ እንደምትቀጥል ሲያሳውቁ ሌሎች ሀገሮችም በዘመቻው ከአሜሪካ ጎን እንዲሰለፉ ጥሪ ማቅረባቸውም ተሰምታል።
በሶሪያ ጉዳይ ከአሜሪካ ጋር የደረሰችበትን ውል ውድቅ ማድረጓን ያሳወቀችውና የትራምፕ አስተዳደርን እርምጃ ያወገዘችው ሩሲያ በበኩሏ የሶሪያን የአየር ጥቃት የመከላከል አቅም እንደምታጠናክርና እንደምታሳድግ አሳውቃለች።
የጸጥታው ጥበቃ ምክር ቤት በጉዳዩ ዙሪያ አስቸኳይ ስብሰባ የተቀመጠ ሲሆን የመንግስታቱ ድርጅት ዋና ጸሀፊ አንቶኒዮ ገተርስ አሜሪካ ጥቃቷን እንድታቆም ተማጽነዋል።
ሶሪያ ዓለማቀፍ ስምምነትን በመጣስ በኬሜካል ጦር መሣሪያ ህጻናትና ሴቶችን ጨምሮ በርካታ ሲቪሎችን ገድላለች የሚሉት ዶናልድ ትራምፕ ግን በሶሪያ ላይ የተጀመረው ጥቃት ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።
ምዕራባውያንና የሶሪያ አማጽያን ከቀናት በፊት ኢድሊብ በሚባለው የሶሪያ ክልል በምትገኘውና ካሀን ሼይኩሁን ተብላ በምትጠራው የሶሪያ ግዛት የበሽር አላሳድ መንግስት የኬሚካል ጦር መሳሪያ እንደተጠቀመ ሲከሱ ሩሲያና የሶሪያ መንግስት ደግሞ ጥቃቱ የተፈጸመው በምዕራባውያን በሚታገዙት አማጽያን ነው ባይ ናቸው።
ፕሬዚዳንት ቡሽና ቶኒ ብሌዬር ሳዳም ሁሴን የኬሚካል ጦር መሣሪያ እንደተጠቀሙ በመክሠስ ኢራቅ ላይ በህብረ ብሔሩ ጦር አማካይነት መጠነ ሰፊ ጥቃት ማስፈጸማቸውና ሳዳምን በስቅላት ማስወገዳቸው አይዘነጋም። ይሁንና ከዓመታት በኋላ የቡሽና የብሌየር ክስ ውሸት ሆኖ መገኘቱ ይታወቃል።
ኢራቅ ግን ከያኔ ጀምራ እስካሁን ድረስ የሽብርተኞች መናኸሪያና የፍርስራሽ ክምር ሆና ቀርታለች።
አሁንስ ነገሩ ወዴት እያመራ ነው?
abbaymedia