አሳዛኝ ዜና እንጋፋው ድምፃዊ መስፍን አበበ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ…

ያዥልኝ ቀጠሮ፣ አይሽ አይሽና፣ መልካም ልደትና ሌሎችም ተወዳጅ ሙዚቃዎችን በጊታር በመጫወት የሚታወቀው ድምፃዊ መስፍን አበበ ትናንት በድንገተኛ ህመም ወደ ቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ከተወሰደ በኋላ ዛሬ ከንጋቱ 11 ሰዓት ገደማ ህይወቱ ማለፉን ለመረዳት ተችሏል።

መስፍን አበበ ከደሴ ወ/ሮ ስህን ትምህርት ቤት ባንድ ጋር በመሆን በተለያዩ የኢትዮጵያ ክልሎች በመዘዋወር ሙዚቃዎችን ይጫወት ነበር፡፡

ቦክስ ጊታሩን በመያዝ 22 ያህል ካሴቶችን ማሳተሙን ከቤተሰቦቹ ለመተዳት ተችሏል።

ባለትዳርና የአንዲት ሴት ልጅ አባት የነበረው የድምፃዊ መስፍን አበበ የቀብር ስነ-ሥርዓት ነገ ከቀኑ በ6 ሰዓት በጴጥሮስ ወጳውሎስ ቤተክርስቲያ ይፈፀማል ተብሏል፡፡

ለመላው ቤተሰቡና ወዳጆቹ እንዲሁም ለኣድናቂዎቹ መጽናናትን እመኛለው።

ጓል ዓጋመ's photo.

About Aseged Tamene
Your rights are your security. When you, 'give up your rights for security", it's not security you get, but slavery.'

Leave a comment