ትግራይ ክልል እራሳችሁን ጠብቁበት ተብሎ ጠብመንጃ ይሰጣል።

914e2-tplf_failing

መቀሌ ዩኒቨርስቲ መምህር በነበርኩበት ወቅት ጏደኛየ እና እኔ ቤት ተከራይተን የምንኖረው ከሁለት ጎረቤት አከራዮች ነበር። እናም አንድ ቀን የጏደኛየ አከራዮች ሰርግ ተጠርተው ወደ አዲስ አበባ ለመሄድ ይወስናሉ። ሰዎቹ በእድሜ ገፋ ያሉ ስለሆነ ትንንሽ ልጆች የሏቸውም ነበርና ወደ አዲስ አበባ ሲሆዱ ቤት የሚጠብቅላቸው ሰው ያጣሉ። ከዚያም ይህ ሰውየ ታጣፊ ክላሹን አውጥቶ ጏደኛየን እንካ ይሄን ይዘህ ቤቴን ጠብቅልኝ አለውና ሰጠው። ልጅም ክላሹን ተቀብሎ ግን እንዲህ ብሎ ጠየቀው” ጠብመንጃ መያዝ እንዴት ተፈቀደልህ አለው” ሰውየውም “እኛ እኮ እራሳችሁን ጠብቁበት ተብለን ጠብመንጃ ይሰጠናል” አለው። ልብ በሉ ይህ ሰውየ የቀበሌ ሊቀመንበር ወይም የመንግስት ስራ አስኪያጅ አይደለም የመንግስት ሰራተኛ እንጅ።

ኤርምያስ ለገሰ በመጽሀፉም እንደጻፈው የወያኔ አባላት የነበሩ 10ሺህ ትግሬዎች ከሰራዊቱ ተሰናብተው የአዲስ አበባ ነዋሪ እንዲሆኑ ሲደረጉ ከነሙሉ ትጥቃቸው ነው። ስለዚህ ትግሬ የታጠቀው ትግራይ ውስጥ ብቻ ሳይሆን አዲስ አበባና በየሚኖርበት የአገሪቱ ክፍል ውስጥ ነው።

አማራ ክልል እንኳን የመንግስት ሰራተኛው አርሶ አደሩ ጠብመንጃ መያዝ አይፈቀድለትም። Gashaw AlemyeAgegne

About Aseged Tamene
Your rights are your security. When you, 'give up your rights for security", it's not security you get, but slavery.'

One Response to ትግራይ ክልል እራሳችሁን ጠብቁበት ተብሎ ጠብመንጃ ይሰጣል።

  1. abe says:

    Kizen atabza , ayzoh minim athonm.

    Like

Leave a comment