ትግራይ ክልል እራሳችሁን ጠብቁበት ተብሎ ጠብመንጃ ይሰጣል።
April 21, 2016 1 Comment
መቀሌ ዩኒቨርስቲ መምህር በነበርኩበት ወቅት ጏደኛየ እና እኔ ቤት ተከራይተን የምንኖረው ከሁለት ጎረቤት አከራዮች ነበር። እናም አንድ ቀን የጏደኛየ አከራዮች ሰርግ ተጠርተው ወደ አዲስ አበባ ለመሄድ ይወስናሉ። ሰዎቹ በእድሜ ገፋ ያሉ ስለሆነ ትንንሽ ልጆች የሏቸውም ነበርና ወደ አዲስ አበባ ሲሆዱ ቤት የሚጠብቅላቸው ሰው ያጣሉ። ከዚያም ይህ ሰውየ ታጣፊ ክላሹን አውጥቶ ጏደኛየን እንካ ይሄን ይዘህ ቤቴን ጠብቅልኝ አለውና ሰጠው። ልጅም ክላሹን ተቀብሎ ግን እንዲህ ብሎ ጠየቀው” ጠብመንጃ መያዝ እንዴት ተፈቀደልህ አለው” ሰውየውም “እኛ እኮ እራሳችሁን ጠብቁበት ተብለን ጠብመንጃ ይሰጠናል” አለው። ልብ በሉ ይህ ሰውየ የቀበሌ ሊቀመንበር ወይም የመንግስት ስራ አስኪያጅ አይደለም የመንግስት ሰራተኛ እንጅ።
ኤርምያስ ለገሰ በመጽሀፉም እንደጻፈው የወያኔ አባላት የነበሩ 10ሺህ ትግሬዎች ከሰራዊቱ ተሰናብተው የአዲስ አበባ ነዋሪ እንዲሆኑ ሲደረጉ ከነሙሉ ትጥቃቸው ነው። ስለዚህ ትግሬ የታጠቀው ትግራይ ውስጥ ብቻ ሳይሆን አዲስ አበባና በየሚኖርበት የአገሪቱ ክፍል ውስጥ ነው።
አማራ ክልል እንኳን የመንግስት ሰራተኛው አርሶ አደሩ ጠብመንጃ መያዝ አይፈቀድለትም። Gashaw AlemyeAgegne
Kizen atabza , ayzoh minim athonm.
LikeLike