የቀድሞው የኢትዮጵያ ፕሬዚዳንት መንግስቱ ኃይለማርያም ‘ትግላችን’ የተሰኘውን 2ኛውን ቅጽ መጽሐፋቸውን ጽፈው ለንባብ አበቁ::

ትግላችን የተሰኘው የኮለኔሉ መጽሐፍ በጸሃይ አሳታሚነት የመጀመሪያው ዕትም ወጥቶ ነበር:: ሆኖም ግን መንግስቱ ኃይለማርያምን የሚቃወሙ ድረገጾች መጽሐፉን በስካነር ኮፒ በማድረግ በነፃ ሕዝብ ጋር እንዲዳረስ በማድረጋቸው አሳታሚው ከፍተና ኪሳራ ላይ ወድቆ እንደበር ይታወሳል:: ኮለኔሉ መጽሐፉን ጽፈው ለአሳታሚው ሲያስረክቡ ገንዘባቸውን የተቀበሉ በመሆኑ ምንም ዓይነት ኪሳራ ባይደርስባቸውም ጸሐይ አሳታሚ ድርጅት ግን ክፍል 2ቱን መጽሐፍ ለማሳተም አልደፈረም ሲሉ የዘ-ሐበሻ ምንጮች ይገልጻሉ::

አዲሱ የኮለኔል መንግስቱ መጽሐፍ በዓይናለም አሳታሚ ድርጅት አማካኝነት የወጣ ሲሆን አሁንም በመንግስቱ ኃይለማርያም ላይ ጥላቻና ተቃውሞ ያላቸው ሰዎች መጽሀፉን በስካን አድረገው በነጻ በየኢንተርኔቱ ይለቁታል የሚለው ስጋት አለ::

ኮ/ል መንግስቱ በቁጥር ሁለት መጽሐፋቸው ” ብርጋዴር ጀነራል ተፈሪ በንቲን የደርጉ ሊቀመንበር ማድረግና ብርጋዴር ጀነራል ጌታቸው ናደውን በቅድሚያ፣ የምድር ጦር አዛዥ በኋላም የኤርትራ ክፍለ ሀገር አስተዳዳሪና የመላው የሰሜን መለዮ ለባሽ ሠራዊት አዛዥ በማድረግ ረገድ የተሰራው ስህተት የማንም ሳይሆን የእኔ ነበር” ሲሉ በጀርባው ሽፋን ላይ ጽፈዋል::

About Aseged Tamene
Your rights are your security. When you, 'give up your rights for security", it's not security you get, but slavery.'

2 Responses to የቀድሞው የኢትዮጵያ ፕሬዚዳንት መንግስቱ ኃይለማርያም ‘ትግላችን’ የተሰኘውን 2ኛውን ቅጽ መጽሐፋቸውን ጽፈው ለንባብ አበቁ::

  1. Pingback: የቀድሞው የኢትዮጵያ ፕሬዚዳንት መንግስቱ ኃይለማርያም ‘ትግላችን’ የተሰኘውን 2ኛውን ቅጽ መጽሐፋቸውን ጽፈው ለንባብ አበቁ:: - EthioExplorer.com

  2. Pingback: የቀድሞው የኢትዮጵያ ፕሬዚዳንት መንግስቱ ኃይለማርያም ‘ትግላችን’ የተሰኘውን 2ኛውን ቅጽ መጽሐፋቸውን ጽፈው ለንባብ አበቁ:: « mabdllselam's Blog

Leave a comment