በኢትዮጵያ አንድ ነጋዴ እስር ቤት እንዳለው ጠ/ሚ/ር ሃ/ማርያም ተናገሩ
March 19, 2016 Leave a comment
በኢትዮጵያ አንድ ነጋዴ እስር ቤት እንዳለው ጠ/ሚ/ር ሃ/ማርያም በግልፅ ተናግረዋል። ቱጃሩ ዛሬ ጡንቻው እንዲፈረጥም ጥርጊያ መንገድ ያመቻቹት በስልጣንና እስር ቤት ይገኛሉ። የደህንነት ሹም ወ/ስላሴና የጉምሩክ ሃላፊ ገ/ዋህድ እንዲሁም በረከት ስሞኦንና አዜብ መስፍን ይጠቀሳሉ። 200 ነጋዴዎች በቱጃሩ ትእዛዝ በጉምሩክ ግቢ በኮንቴነር ውስጥ እንዲታሰሩ ያደረገው ገ/ዋህድ (የተጠቀሱት ባለስልጣናት ተባብረዋል) ድብደባ ይፈፅምባቸው ነበር። ፍ/ቤት ፍታ ሲለው አንፈታም ብሎ በአደባባይ ተናገረ። ከታሳሪዎቹ በድብደባ ጆሯቸው ይመግልና ይሰቃዩ እንደነበር ቢገልፁም ሰሚ አልተገኘም፤ የፍ/ቤት ውሳኔ አልተከበረም። 2 ነጋዴዎች የገዛ ህይወታቸውን እንዲያጠፉ ተደርጓል። የሪፖርተር ጋዜጣ አዘጋጅ በመፃፉ ብቻ በጠራራ ፀሀይ የግድያ ሙከራ ተፈፀመበት። ድርጊቱን የፈፀሙ በቦሌ የሸኙት በረከትና ወ/ስላሴ ነበሩ። በቢሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ ከባንክ ቱጃሩ እንዲበደሩ ፍቃድ ሲሰጡ የቆዩት በረከት ናቸው። ..ብዙ ማስረጃና መረጃ ማቅረብ ይቻላል። ቢዘገይም ጠ/ሚ/ሩ ሀቁን አፍርጠዋል፤ እርምጃ ባይወሰድም! በአንፃሩ በቀለ ገርባ፣ እስክንድር ነጋ፣ ተመስገን ደሳለኝ፣ አብርሀ ደስታና ሌሎች ንፁሀን “ህግ ይከበር! መናገርና መፃፍ መብት ይጠበቅ! ግድያና እስር ይቁም!” ብለው በሰላማዊ መንገድ በመጠየቃቸው ከነወ/ስላሴ ጋር እስር ቤት እንዲማቅቁ ተደርገዋል። ሃ/ማርያም ዛሬ ያመኑትን ጉዳይ እነዚህ ወገኖች ለአመታት ሲጮሁበት ከርመዋል። ..ነጋዴው የእግር ኳስ ክለብ ከማፍረስ እስከ እስር ቤት ማቆም ደረሰ።ነገ ደግሞ መንግስት ላለማቆሙ ማረጋገጫ የለም። ለነገሩ እስር ቤት አስቀድሞ ማቆሙ ..