ህዝብ የመረጣቸው ኮሚቴዎቹን በመነጣጠል በባዶ ወረቀት በግድ በፖሊስ ፈርሙ እየተባሉ መሆኑ VOA ዘገበ፡፡

በማይካድራ የሚገኙ ሰዎችን/ ጋዜጠኛ ሰለሞን አባተ በስልክ እንዳናገራቸው ሳጅን ሀጎስ እና ሀይሌ የተባሉ ፖሊስ በባዶ ወረቀት የማትፈርም ከሆነ ወደ ጭቃ አስገባሀለሁ ትሞታለህ እያሉ ዛቻና ወካባ እያደረሱብን ይገኛል ሲሉ ገለጹ፡፡
የወልቃይት ህዝብ ቀደም ሲል ጀምሮ አባት ቅድመ አያት የአማራ ማንነት እንጂ እነሱ ባሉት ክልል አንጠራም ያሉት ኮሚቴው የጠየቃችሁትን ጥያቄ አቁመናል በማለት የማትፈርሙ ከሆነ ዋጋህን ታገኛለህ እየተባሉ መሆኑ ተናግረዋል፡፡
/ጋዜጠኛ ሰለሞን አባተ ይሄን ቃለ መጠይቅ በራዲዮ ባስተላልፈው ችግር ይፈጥርበዎት ይሆን? ብሎ ለጠየቃቸው)) “ለምን አይቆራርጡኝም! ለምን አልሞትም! ለምን እንደፈለጉ አያደርጉኝም! የወልቃይት ህዝብ የማንነት ጥያቄ እውነትን ይዘን ነው፡፡ እንደፈለጉ ያድርጉኝ በማለት ሲናገሩ ስማቸውን ለጠየቃቸው በግልጽ ነገረውታል የወልቃይት ህዝብ የማንነት ጥያቄ የጸረ ሰላም የግንቦት 7 ጥያቄ ነው እያሉ ለማሸማቀቅ ቢሞክሩም እስከመጨረሻ ድረስ ጥያቄ ከመጠየቅ አንዳችም ነገር አያግደንም ሲሉ ተናግረዋል፡፡ ለጆግኖች የወልቃይት ህዝብ ለሚደርስባቸው ችግር ድምጽ እንሁን፡፡
ብዙ የአምባገነኑ የትግራይ አስተዳደር ሴራ ይጠብቅሃልና
በማጭበርበር ቅጥ ያጣው የትግራይ አስተዳደር ሰዎችን በትናንሽ ጥቅማጥቅሞችን በማታለል ወልቃይት ትግራይ ነው የሚል ፔትሽን እያሰባሰበ ይገኛል፡፡ ስለሆነም ማንኛውም የወልቃይት ተወላጅ በማንኛውም መስሪያ ቤት ሲገባ /የሚፈርምበት አጋጣሚ ካለ የሚፈርምበት(ፎርም) ወረቀት ምንነቱን ጠንቅቆ ማንበብ አለበት፡፡
( እኛ የወልቃይት ህዝብ ይህን የተፈጠረውን የትምከተኝነትና የጠባብነት አስተሳሰብ የማንነት ጥያቄ የህዝብ ጥያቄ ስላልሆነ የህዝብ ውክልና የሌላቸው ጥገኛ ሃይሎች የሚያነሳሱት በመሆኑ መንግሥት ከነዚህ ላይ እርምጃ እንዲወሰድ በጥብቅ እናሳስባለን ፡፡ እኛ የግል ማንነታችን እናውቃለንም በህገ መንግሥታችንም ተመልሶልን ያደረ ነው፡፡ ይላሉ)
ድል ለወልቃይት ህዝብ!!!”
ውድቀት ለአምባገነኑ የትግራይ አስተዳደር!!!

About Aseged Tamene
Your rights are your security. When you, 'give up your rights for security", it's not security you get, but slavery.'

Leave a comment